• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

48 + 1 ደቂቃ ቢያልፍ ምን እንደሚከተል ግንዛቤ ነበር

October 11, 2014 03:28 am by Editor Leave a Comment

ከስያሜው ጀምሮ እያነጋገረ ያለው የኢህአዴግ የአሜሪካ ጽ/ቤት የጥበቃ ሰራተኛ፣ በኢህአዴግ አባባል “ዲፕሎማት” አገር ለቆ እንዲወጣ ከተሰጠው የጊዜ ገደብ አንድ ደቂቃ ቢዘገይ ምን ሊከተል እንደሚችል አስቀድሞ ከስምምነት ላይ ተደርሶ እንደነበር ተጠቆመ። በስምምነቱ መሰረት ወዲ ወይኒ መባረሩ ከህወሃት ደጋፊዎችና አመራሮች ቅሬታ ማስነሳቱን አስመልክቶ አንድ ከፍተኛ የአሜሪካ ዲፕሎማት “ወያኔዎቹ የተሰራላቸው ውለታ አልገባቸውም ማለት ነው” ሲሉ መደመጣቸውን የጎልጉል ታማኝ ምንጭ ተናገሩ።

ለተቃውሞ ወደ ኢህአዴግ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ባመሩ ኢትዮጵያኖች ላይ ጥይት የተኮሰው የቀድሞው “ዲፕሎማት” ተመልሶ አሜሪካን መርገጥ እንዳይችል ተደርጎ የተባረረው በሁለቱም ወገኖች በተደረገ የውስጥ ስምምነት ነው። ለጉዳዩ እጅግ ቅርብ የሆኑ እንደገለጹት በአሜሪካው የምስጢር አገልግሎት (Secret Service) እና የዋሽንግተን ከተማ ፖሊስ ወዲ ወይኒን ለማሰር ወስነው ነበር። ውሳኔው ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት እነ አቶ ግርማ ብሩ “ጓዳቸውን” ፈቅደው ለማሰናበት ቅድሚያውን በመውሰዳቸው ተጠርጣሪው ወንጀለኛ ሳይያዝ ቀርቷል። ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መ/ቤት (State Department) የተሰጠው መግለጫም ቃል በቃልም ባይሆን ይህንኑ ያረጋገጠ ሆኗል።

የምስጢር አገልግሎቱም ሆነ የከተማው ፖሊስ ከ“ፖለቲካው ግንኙነት” ጋር በተያያዘ ስለሚፈጠረው የፖለቲካ ውዝግብ ቁብ እንደሌለው ስለ አሰራሩ የሚያውቁ ይናገራሉ። ይሁን እንጂ አቶ ግርማ ብሩ “በዲፕሎማሲያዊ ቋንቋ ተነጋግረናል” ሲሉ ለአገዛዙ ተላላኪ ድረገጽ ባለቤት እንዳረጋገጡት የስቴት ዲፓርትመንት ሰዎች የጊዜ ገደብ በማስቀመጥ ያልተፈረደበትን ወንጀለኛ፣ ወዲ ወይኒን፣ ካገር የሚወጣበትን መንገድ እንዳመቻቹ ዲፕሎማቱ አልሸሸጉም።

“አሜሪካ በቂ ጥበቃ አላደረገችልንም” በማለት ተቃውሞ የሚሰነዝሩት አፍቃሪ ህወሃቶች የሚሰነዝሩትን ተቃውሞ አስመልክቶ “የተደረገላቸውን ውለታ ካለመረዳት ነውነው፤ አፋቸውን ቢዘጉ (ዝም ቢሉ) የተሻለ ነው” ሲሉ የተደመጡት ከፍተኛ ሃላፊ፣ ይህንን ሲናገሩ ክፉኛ ተበሳጭተው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል። የአሜሪካ መንግስት ተወንጃዩ ፍርድ ቤት ቀርቦ የሚዲያ ቁርስና ምሳ ሲሆን፣ ከዚሁ በጋር ከኢህአዴግ ጋር የሚነሳው ውዝግብና በምስራቅ አፍሪቃ በኩል ስለሚከወነው የፖለቲካ ጨዋታ ሲባል ጉዳዩ አሁን በተከናወነበት መልኩ እንዲጠናቀቅ መወሰኗን ከጉዳዩ ብዙ ርቀት የሌላቸው ክፍሎች አመልክተዋል። አቶ ግርማም ቢሆኑ “በዲፕሎማሲያዊ” ሲሉ ቋንቋውን ቢያስውቡትም ስምምነቱ ስለመኖሩ ከማሳበቅ ወደኋላ አላሉም።

በገደብ፣ በስምምነት የተቆረጠው 48 ሰዓት ቢተላለፍ ምን ሊከተል እንደሚችል ግንዛቤ በመኖሩ እነ አቶ ግርማ ወዲ ወይኒን አፋፍሰው ኢህአዴግ አለገደብ ወደሚገዛት አገር ልከውታል። ይህ ሳይሆን ቀርቶ አንድ ደቂቃ ቢዘገይ “ወዲ ወይኒ ወህኒ ወርደው ወዲ ወህኒ የሚል ስም ይሰጣቸው ነበር” ሲሉ ከዲሲ አካባቢ አንዳንዶች ተሳልቀዋል፡፡

ከኢህአዴግ ወገን አሁንም ዋሽንግተን ዲሲ ለተከራዩት ለጽህፈት ቤታቸው አሜሪካ ልዩ እንክብካቤ እንዲደረግ እየወተወቱ ነው። አሜሪካ ለዚህ ምንም ዓይነት የተለየ ጥበቃ የማታደርግ መሆኑ በተለያዩ መግለጫዎች የተነገረ ቢሆንም በህወሃት/የኢህአዴግ በኩል ጥያቄው እንዲነሳ ያደረገው መነሻ በድጋሚ ተመሳሳይ ውርደት እንዳይከሰትና ወደ ሌሎች አገራትም እንዳይዛመት ስጋት በመኖሩ ነው።

በተመሳሳይ ዜና ከአሜሪካ በሰዓታት ገደብ እንዲሰናበት የተደረገውና ተበደልን ባሉ ወገኖች ላይ ጥይት ሲተኩስ የነበረው ይኸው የትግራይ ተወላጅ ለሞራሉ በሚል ወደ ሌላ አገር ኤምባሲ ተዛውሮ እንዲሰራ አዲስ ምደባ እንደሚሰጠው የጎልጉል የውጪ ጉዳይ ምንጮች አመልክተዋል። ከህወሃት ከፍተኛ ባለስልጣን ወጣ የተባለው ይኸው የአዲሱ ምደባ ጉዳይ ለወዲ ወይኒ “ተጋዳላይነት”፤ ለሌሎች ደግሞ “አለኝታነትን ለማሳየት” በሚል ታስቦ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule