• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከተማርኩት ቁጥር 1

March 12, 2016 05:41 am by Editor 2 Comments

ያሜሪካ ቆይታዬ በጣም አጭር ነው። ሁለት አመት እንኳን አይሞላም። ላገሩ አሁንም ላገሩ ባዳ ለወንዙ እንግዳ ነኝ። ገና ብዙ ያልገባኝ ነገር አለ።

ግን በዚህች አጭር ጊዜም ቢሆን ብዙ ጠቃሚ ነገር ተምሬያለሁ ብል “አይ ገና ምኑ ተይዞ” እንደማትሉኝ ተስፋ አደርጋለሁ። ለምን ቢባል ልማር ላለ ሳር ቅጠሉ እውቀት መሆኑን ታውቁታላችሁ ብዬ ነው። ይልቅስ ለመሆኑ ምን ተማርክ ብትሉኝ ወጌን እጀምራለሁ።

አዎ! ብዙ ነገር። ከእንግዲህ ምናልባት ሰሚ ካገኘሁ ከተማርኩት እያልኩ በተከታታይ አንዳንድ ነገር ለማካፈል አቅጃለሁ። ታዲያ እኔ ትምህርት አገኘሁበት ያልኩት ነገር ከታወቀ የቆየ ወይም የፊደል ቆጣሪ ግንዛቤ ሆኖ ካገኛችሁት የሞተውን አባባ ይለዋል ወይም የልጅ ነገር ሳትሉ ሃሳብ ስጡበት። እኔ አላማዬ መማር ስለሆነ ከስህተቴ እማራለሁ።

ከተማርኩት ቁጥር 1

ወደፍሬ ነገሩ ከመግባቴ በፊት ተማርኩባቸው የምላቸው ጉዳዮችን የማነሳው ሀገሬ ኢትዮጵያን በሆዴ ይዤ መሆኑን ልብ በሉልኝ። ባጭሩ መሰረታዊ ጉዳያችን ታላቋ ኢትዮጵያ (ለኔ ዛሬም ኢትዮጵያ ታላቅ ናት) ከታላቋ አሜሪካ ህይወት ምን ልትማር ትችላለች የሚል ነው።

ስለ ጦርነት

አሜሪካኖች እርስበርእሳቸው ተዋግተዋል። ለአምስት አመት። ከ600 ሽህ ህዝብ በላይ አልቋል። ልባአድርጉ! የተዋጉት እርስበርስ ነው። ከዚህ የታሪክ ክስተት መነሻና መድረሻ ለሀገራችን ጉዳይ የሚጠቅም ቁም ነገር ማግኘት ይቻላል። በመጀመሪያ ኢትዮጵያውያን እርስበእርሳችን ስንዳማ መኖራችን የሚያስመሰግን ባይሆንም ካለም ለይቶ የሚያስረግመን ገጠመኝ አይደለም። በዘመኑ የተሻለ ስልጣኔ የነበራቸው አሜሪካኖች ዴሞክራሲያዊ የሚባል ስርአት ከገነቡ በኋላ እንኳን በዚያን ጊዜ ባስከፊነቱ ወደር አልባ የነበረ እልቂት ያስከተለ ጦርነት አካሂደዋል። ከዚህ አንፃር ሲታሰብ የኢትዮጵያውያን ልምድ ባይወደስም ጉድ ሊባል አይገባም።

ከዚህ ሁሉ የበለጠው ትምህርት ግን ጦርነትን የታሪክ ትምህርት እንጂ የዘወትር የጀግንነት ስራ አድርጎ ያለመቀጠል ነው። አሜሪካኖች ጦርነቱን ታላቅ ሀገርና ጠንካራ የፍትህ ስርአት ገንብተውበታል። ዳግመኛም አላካሄዱትም። ጦርነታቸውን ሌላ ጦርነት የማያስነሳ ስርአት መሰረቱበትና ታሪክ ብቻ ሆኖ እንዲቀር አደረጉት። እኛም ማድረግ ያቃተንና ማድረግ ያለብንም ይህንን ነው። መኮነን ያለብን ያሳለፍነውን ጦርነት ሳይሆን የሚመጣውን አዲስ ጦርነት ነው። አሜሪካኖች አንድ ጊዜ ደም ተፋሰው የጦርነትን በር ዘጉ። እኛ የታሪክ ጦርነቶችን እያብሰለሰልን ላዲስ ጦርነት ጠመንጃ እንወለውላለን። ልዩነታችን እዚህ ላይ ነው። በጦርነት ስልጣን የያዘው አካል ጦርነት በታሪክ ያደረሰብንን ጉዳት በማጤን ዳግም ደም አፋሳሽ ግጭት እንዳይነሳ ለሰላምና ለህዝብ ደህንነት በግንባር ቀደምትነትና በሆደሰፊነት ጠንክሮ ከመስራት ይልቅ ወንድ የሆነ ይምጣ አይነት ፉከራን ያሰማናል። እንዲያውም ራሱ ቀድሞ በራሱ ህዝብ ላይ ጦርነት አውጆ ህዝብ በከፈለው ግብር ጥይት እየገዛ ህዝብ ላይ ይተኩሳል። ሌላው በበኩሉ ለነፃነትና ሰላም መፍትሄው ጠመንጃ ነው በሚል አቀባብሎ ደም ሸቶኛል ይላል።

ዳያስፖራውም ቢሆን ቢያንስ ጦርነት አከል ንግግር አላጣም። እና ሁላችንም ተደምረን ስንሰማ ዜማችን አንድ ነው። ይሄውም፤ ትናንት ስንዋጋ ነበር፤ ዛሬም እንዋጋለን፤ ነገም እንዲሁ፥ የሚል ነው። ክፉ አባዜ!

አሜሪካኖች ከጦርነት ዘላቂ ሰላም፣ ነፃነትና ፍትህን ሲመሰርቱ እኛ ከጦርነት ተነስተን ወደ ጦርነት እንጓዛለን። አሜሪካኖች ከጦርነት ልማትን ተምረው ሰላማዊ ስርአት ሲመሰርቱ እኛ ግን ከጦርነት ለነገ የሚሆነንን አዲስ ጥፋት እንቀስማለን።

እኔ ግን የተማርኩትና ያገሬ ሰውም እንዲማር የምመኘው ከጦርነት ጥፋትን ሳይሆን ደህንነትን፣ ከግጭት ቂምን ሳይሆን ፍቅርን፣ ከስህተት ስህተትን ሳይሆን እርምትን እንማር ዘንድ ነው። እናም እኔ ካሜሪካኖች ታሪክ የተማርኩት የመጀመሪያው ቁምነገር ይህንን ነው። ሌላውን ሌላ ጊዜ ማንሳቴ አይቀርም። ሰላም ሁኑልኝ፡፡

ህሩይ ደምሴ

ከዋሽንግተን ዲሲ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. eunetu says

    March 18, 2016 04:03 pm at 4:03 pm

    ወንድሜ ህሩይ

    በወገኔና በአገሬ ላይ ከገጠመኝና አልወለድ ካለ የጽንስ ምጥ የገላገልከኝ መሰለኝ!ለካ እንዲህ እንዳንተ ያሉ ቅን ሃሳብ ያላቸው ወንድሞች በየቦታው አሉ በማለት ከእንቅልፌ ነቃሁ! በርታ ወንድሜ! አብረን እንጬህ በጎ የሆነውንም በተግባር እናሳይ!በለው፣ አሳደው፣ ድፋው፣ አሳየው፣ ፉከራው፣ ጥላቻውና መነቋቆሩ ወዘተ የትም አላደረሰንምና በፍቅር ለሁለንተናዊ የዘመናት ችግራችን በጋራ ምክክር አብረን ለበጎ ሥራ እንነሳ???

    ይህችን አባባልህን ወደድኳት:

    እኔ ግን የተማርኩትና ያገሬ ሰውም እንዲማር የምመኘው ከጦርነት ጥፋትን ሳይሆን ደህንነትን፣ ከግጭት ቂምን ሳይሆን ፍቅርን፣ ከስህተት ስህተትን ሳይሆን እርምትን እንማር ዘንድ ነው። እናም እኔ ካሜሪካኖች ታሪክ የተማርኩት የመጀመሪያው ቁምነገር ይህንን ነው። ሌላውን ሌላ ጊዜ ማንሳቴ አይቀርም። ሰላም ሁኑልኝ፡፡

    መልካም ፈቃድህ ከሆነ በኢሜል ተገናኝተን በመመካከር ለምስኪኑ ወገናችን ሰላም በእግዚአብሔር ስም በጎ ሥራ አብረን እንሥራ: eunethiwot@gmail.com

    የፍቅር አምላክ በመለኮታዊ ፍቅሩ በጽሑፍህ ላይ ከገለጥከው በበለጠ መልኩ:
    ለራሱ ክብር!
    ለምስኪኑ ወገንህ ጥቅምና ሰላም!
    ለክፉው ደግሞ መዋረድ!
    በሃይልና በስልጣን ይግለጥህ!!!

    ይህ ከሆነ ሕልምህ እኔም አብሬህ ነኝ!!!

    በእውነት ወንድምህ

    እውነቱ ነኝ

    Reply
  2. Yikir says

    March 29, 2016 09:31 pm at 9:31 pm

    Mikirih melkam new hizibum yaminal. Hulum sew Mihur Mehayimu yemisasatew neger:- Ethiopian yemimeraw akal Satan /LUSIFER MEHONUN / YIZENEGALU. Wendime eski hasabihin le Lusiferu asredaw.KETEKEBELEH WEDE AGANINTINET ZIK BILOWAL MALET NEW 10 % KETEGEBERE JINI HONWAL MALET NEW. 50 %ketekebeleh yih jini tamo yihonal.ANTE YALKEWIN 90% KETEKEBELE YIH JINI MOTOWAL MALET NEW. Lije berta jiniw bimot le Ethiopiachim melkam new.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule