• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ብሄድም እመለሳለሁ”

June 13, 2015 05:33 am by Editor 3 Comments

በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት አራተኛ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ዌንዲ ሸርማን ሰኔ 23፤ 2007 ዓም ከሥልጣናቸው እንደሚለቁ ከተሰማ ጥቂት ሳምንታት የተቆጠሩ ቢሆንም ተመልሰው በከፍተኛ ባለሥልጣንነት ሊመጡ እንደሚችሉ ተጠቆመ፡፡

ከጥቂት ወራት በፊት በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ያደረጉት ሸርማን በወቅቱ ከቴድሮስ አድሃኖም ጋር ጋዜጣዊ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ያሰሙት ንግግር ከፍተኛ ተቃውሞ አስነስቶባቸው ነበር፡፡

ባለሥልጣኗ ፈጽሞ ባልተጠበቀ ሁኔታ ለኢህአዴግ በካድሬ ደረጃ ሙገሳ ቸረው ነበር፡፡ ኢህአዴግ በሚገዛት ኢትዮጵያ ያለውን ህዳሴ ካወደሱ በኋላ ኢትዮጵያ በዴሞክራሲያዊ መንገድ በተመረጠ አስተዳደር ሥር እንዳለች ተናግረው ነበር፡፡ በመቀጠልም ይህንን በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠን በኃይል ለመጣል የሚንቀሳቀሱ በሙሉ ሊጠነቀቁ እንደሚገባቸው አሳሰቡ፡፡ ሲቀጥሉም ግንቦት ሰባትን በስም በመጥራት ሌሎችንም የኃይል እርምጃ በመውሰድ ለውጥ ለማምጣት ለሚፈልጉት ኃይላት ሁሉ “አሸባሪዎች” ናችሁ የሚል መልዕክት አስተላለፉ፡፡

ከዚህ የዌንዲ ሸርማን ንግግር በኋላ በተለይ በሰሜን አሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ መንገዶች ተቃውሟቸውን ማሰማታቸው ይታወሳል፡፡ ካቀረቧቸው ጥያቄዎችም መካከል ባለሥልጣኗ ይቅርታ እንዲጠይቁ፣ ከሥልጣን እንዲነሱ፣ ወዘተ የሚሉት ጥቂቶቹ ነበሩ፡፡

ለሳምንታት የዘለቀው ተቃውሞ ጋብ እንዳለ ባለፈው ሰሞን ዌንዲ ሸርማን አሁ ካሉበት ሥልጣን ሰኔ 23 (ጁን 30) እንደሚለቁ ደብዳቤ አስገብተው መጽደቁን ይፋ አደረጉ፡፡ አለቃቸው ጆን ኬሪና ፕሬዚዳንት ኦባማ የሸርማንን ታላቅነትና የአገልግሎት ዘመን በማወደስ ታላቅ ሙገሳን ቸሯቸው፡፡

ዜናው በበርካታ ኢትዮጵያውያን ዘንድ የተቀናጀ ትግል ውጤት እንደሆነ ተደርጎ ሲወሰድ ተሰምቷል፡፡ በአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መ/ቤት ላይ ኢትዮጵያውያን ያደረጉት ተጽዕኖ እንዳለ ሆኖ የዌንዲ ሸርማን አሁን ከሥልጣን መልቀቅ ምናልባት ራሳቸውን ለከፍተኛ ሥልጣን ለማዘጋጀት ነው የሚሉም አሉ፡፡

በቢል ክሊንተን የአስተዳደር ዘመን በውጭ ጉዳይ መ/ቤት ሥራቸውን የጀመሩት ሸርማን፤ የሒላሪ ክሊንተን የቅርብ ወዳጅ ናቸው፡፡ ሸርማን አሁን ላሉበት ከፍተኛ የሥልጣን ቦታ በ2011ዓም ብቁ ያደረጓቸው በወቅቱ የውጭ ጉዳይ መ/ቤቱን የመሩት ሒላሪ ክሊንተን ነበሩ፡፡ ወ/ሮ ክሊንተን በመጪው የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ከሁሉም በብቃት ላይ የሚገኙ ተወዳዳሪ ሆነው ቀርበዋል፡፡ የማሸነፋቸውም ዕድል ከፍተኛ እንደሆነ በብዙዎች እየተጠቆመ ነው፡፡

ዌንዲ ሸርማን ባሁኑ ወቅት ከሥልጣን የለቀቁበት ተደርጎ የተወሰደው ቀዳሚው ምክንያት የኑክሌር መሣሪያዎችን በተመለከተ ከኢራን ጋር ይካሄድ የነበረው ድርድር ወደ መጨረሻው በመድረሱና ሴኔቱ ረቂቅ ሕጉን በማጽደቁ እንደሆነ በስፋት ተነግሯል፡፡ ሆኖም ግን የርሳቸው ቦታ ለኑክሌር ድርድር ተብሎ ብቻ የተቀመጠ የሥልጣን እርከን እንዳልሆነ ይታወቃል፡፡

ከክሊንተን ቤተሰብ ጋር የጠበቀ ወዳጅነት እንዳላቸው የሚነገረውና በኒውዮርክ ከታዋቂ ይሁዲ ቤተሰብ የሚወለዱት ሸርማን ሒላሪ ክሊንተንን በምርጫ ዘመቻቸው ላይ የውጭ ጉዳይን በተመለከተ በማማከርና በመሥራት ሊያገለግሉ ይችላሉ ከሚለው አስተያየት አኳያ ምናልባት ከሥልጣን መልቀቃቸው ታስቦ የተደረገ ነው የሚሉም አሉ፡፡ ይህ ከሆነ እና ሒላሪ ክሊንተን የፕሬዚዳንታዊ ምርጫውን አሸንፈው ነጩ ቤተመንግሥት የገቡ ዕለት ለከፍተኛ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ወይም በተባበሩት መንግሥታት የአሜሪካ አምባሳደርነት የሚሾሙት ዌንዲ ሸርማንን ሊሆን ይችላል፡፡

አሁን ከሥልጣን ሲለቁ ወደ መንግሥታዊ የሥልጣን እርከን የማይመለሱ የመሰለው የዌንዲ ሸርማን ጉዳይ ቀን ጠብቆ የተቃዋሚውን ኃይል ይበልጥ ሊጎዳ የሚችል እንደሆነ ለጎልጉል አስተያየታቸውን የጠቆሙ ገልጸዋል፡፡ ምክንያቱም እርሳቸው አሁን ከኢህአዴግ ጋር ካላቸው ይህንን የመሰለ ቁርኝት አኳያ ወደፊት ከፍ ያለ ሥልጣን ይዘው ብቅ ካሉ በተቃዋሚው ኃይል እንቅስቃሴ ላይ የሚያመጡት ተጽዕኖ እጅግ የከፋና የከረረ ሊሆን ይችላል፡፡

“ብሄድም እመለሳለሁ” የሚመስለው የዌንዲ ሸርማን የሥልጣን መልቀቅ ጉዳይ ከአሜሪካ የፖለቲካ አዘዋወር ጋር ወደፊት በሂደት የሚታይ ቢሆንም የተቃዋሚው ኃይል በተለይ በውጭ ያለው አስቀድሞ ሊሰራው የሚገባው የቤት ሥራ እንዳለ ጠቋሚ ነው፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. melak says

    June 13, 2015 04:34 pm at 4:34 pm

    Let she come again. We will wait her under a strong Ethiopia, or if delayed somehow, on the road towards a strong Ethiopia. America is committing another historical blunder in Ethiopia and East Africa. But I don’t think USA is ignorant of the current political, economic, and social situation unfolding in the country very fast today. What matters is only unity among Ethiopians for a shared goal-overthrowing woyane to begin with.

    Ethiopia will rise again!!! Green, Yellow, and Red

    Reply
  2. Terminator says

    June 13, 2015 11:18 pm at 11:18 pm

    As in Ethiopian I will not vote for Mrs, Clinton because of the vote she while she was a senator for Ethiopian HR 2003 .not only that it her husband who put the infuriate complex ridden Tygerias in power for 24 years not only that he took 20 million dollars from Al modie in the name of charity.

    Reply
  3. Jonathan Takele says

    June 14, 2015 12:43 pm at 12:43 pm

    Shalom Ethiopians in USA:- I recommand the system like the Jewish and Isralis did, Ethiopians in USA almost 2.5 millions according to some datasn out of this data almos 1 milion they have USA citizenship and have full right to do vote for both parties so the answer on your hand just the next general election do your homework don’t give up your voice both of the parties start the campaign soon.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule