• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ብክነትና ምክነት

April 21, 2016 01:32 am by Editor Leave a Comment

በኢትዮጵያ ውስጥ ገንዘብ የሚያባክን ማን እንደሆነ እናውቃለን። ጊዜም የሚያባክነው ማን እንደሆነ ሳናውቅ አንቀርም። እንዲሁም ወንድና ሴት እንደየተፈጥሯቸው እንዳይወልዱ የሚያመክናቸው ምን እንደሆነ አሳምረን እናውቃለን። አንናገርም እንጂ። ምሁራንንስ የሚያባክንንና የሚያመክን ማነው? ጎበዝ ማለት ይህን የሚያውቅ ነው። እኔም ማወቅ የምፈልገው ያገሬን ምሁራን የሚያባክንብኝና የሚያመክንብኝ ማን እንደሆነ ነው።

ሰሞኑን ያዲስ አበባው መንግስት ቀለም ቀለም ሲሸተው ጊዜ እኔንም እንዲሁ ቀለም ቀለም ስለሸተተኝ ስለምሁራን ብንጫወት ምናለ ብዬ ለዛሬ ቁም ነገሬ እንዲሆን መረጥኩት፤ የኢትዮጵያ ምሁራን ጉዳይ፤ በተለይ ያቋማቸውና የጥቅማቸው ጉዳይ። በይበልጥ ደግሞ እንዲያው እንደዋዛ የመባከናቸው ነገር። ባክነዋል እንዴ? ካላችሁ መልሴ እንክት ነዋ!   የሚል ነው። ላስረዳ። የምናገረው ባሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ምድር ስላሉ ምሁራን መሆኑን ልብ በሉልኝ። የውጪዎቹማ  እንዲያው እንዳይቆጡኝ ድምፃችሁን ዝቅ አድርጋችሁ አንብቡልኝ እንጂ እነርሱማ የባከኑት ገና ዱሮ ካገር ከወጡበት እለት ጀምሮ ነው።

ታዲያ ምሁር ማነው? እስከ ስንተኛ ክፍል የተማረ ነው? ምናምን አትበሉኝ። ከመንግስት ጋር የሚያጣላ ጥያቄ አልወድም። በቃ ምሁር። ይገባችኋል። ለምሳሌ ባለፈው በአሜሪካ ድምፅ አማርኛው አገልግሎት ቀርበው በኢትዮጵያ ወቅታዊ ይዞታ ላይ አስተያየትና ትንተና የሰጡትን ከአዲስ አበባ ዩኒበርሲቲ የህግ፣ ሶሲዮሎጂና የፖለቲካ ትምህርት ምሁራን አይነት ማለት ነው። ስም አልጠራም።

ምሁራን በሰው ልጅ እድገት ታሪክ ውስጥ የተጫወቱትን ሚና መዘርዘር ጊዜ ስለሚፈጅ ብቻ ሳይሆን እኔም ስለማላውቀው አናነሳውም። ግን አለምን ለውጠዋል፤ አቅጣጫዋንም ወስነዋል፣ ሲባል ስለሰማሁ እኔም እንዲያ ብንል ዋስ ጥራ የሚለን ያለ አይመስለኝም። በተለይ ከ18ኛው መቶ ክፍለዘመን ጀምሮና ምናልባትም ከዚያም በፊት በየዘርፉ የተቀመሩት ሳይንሳዊ ንድፈሃሳቦችና ግኝቶች ሰውን ዛሬን እንዲመስል አድርገውታል። በተለይ በመንግስታዊ ያስተዳደር ጉዳይና የፖለቲካ ጥያቄዎች አቅጣጫ እንደየሀገሩ ተጨባጭ ሁኔታ አወንታዊም አሉታዊም ሚና ተጫውተዋል። ባንፃሩ ደግሞ ምንም ፋይዳ ያለው ስራ ሳያከናውኑ እንዲያውም ለክፉ ገዢዎች መሳሪያ አቀባይ ሆነው ያለፉበት ታሪክም ይኖር ይሆናል። መሰረታዊ ጥያቄው የቱ ሀገር በምን አኳኋን ተጠቀመባቸው የሚለው ነው። የት ባከኑ? የትስ መከኑ? በማለት መጠየቅ ማለት ነው። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ምሁራን ጠቅመውናል? በፖለቲካው ምዳ ሚና ኖሯቸው ካልጠቀሙን ባክነዋል ማለት ነው። ምናልባትም መክነዋል።

በኔ አስተያየት በተለይ ባለፉት 40 የምጥ አመታት ምሁራንን ሳንጠቀምባቸው ባክነዋል። ያባከናቸውም መንግስት ነው፤ ያለውም የሄደውም። ደርግ ከፊሉን በመግደል ቀሪውን ደግሞ በውድም በግድም አባሪ በማድረግ እውቀታቸውን አባከነው። ብዙዎቹም የሀገራቸው ጉዳይ ሆዳቸውን እያመማቸውና አንጀታቸው እያረረ በምሁርነት ካባቸው ላይ መንግስታዊ መለዮ ደርበው ከእገሌ ጋር ወደፊት እንዲሉ ተገደዱ። ቀሪዎችም ሲያቀብጣቸው (ወይም ሲፈርድባቸው ማለት ይሻል ይሆናል) ለምን አሉና ተገደሉ። ባከኑ ማለት ይሄ አይደል? ወግነው የተረፉትም ተቃውመው የጠፉትም ያው ባክነዋል።

ዛሬስ? ዛሬም ቢሆን ታሪክ እምብዛም የተለወጠ አይመስልም። እንደመጥምቁ ዮሃንስ በበረሃ ያለሰሚ የሚጮኹ ሀቀኛ ምሁራን መኖራቸው ሳይካድ ብዙሃኑ ግን ወይ ለሆዱ ያለዚያም ለባለክንዱ አድሯል። ቀሪውም ጭልፊት እንዳየች ጫጡት በየተቋሙ ጎሬ አድፍጧል። የቀናውም ይብላኝልሽ ሀገሬ ብሎ ካገር ፈርጥጧል። እናም ሁሉም ባክነዋል።

ልማታዊ ምሁራኑ ሳይንስ፣ መንግስትና እድገት አንድም ሶስትም ናቸው በሚል ተጠምቀው 11 ሚሊዮን ህዝብ በርሃብ በሚያጣጥርባት ኢትዮጵያ 11 ጊዜ አድገናል ይሉናል። ማንም ሰው በማንነቱ መብት አለው የሚለውን የቀለም ትምህርት በላፒስ አጥፍተው ማንነት በሞት በሚያስቀጣባት ሀገር የብሄር መብት ተከበረ ይሉናል። ታዲያ ከዚህ በላይ ብክነትና ምክነት ከየት ይመጣል?

እዚህ ላይ መቼም አንተስ በኢህአዴግ አፍንጫ ስር ብትሆን ኖሮ ውዳሴ መንግስትን ከመድገም ሌላ ምን ታደርግ ነበር የሚል ተፈታታኝ አንባቢ መኖሩ አይቀርም። እኔም ባልሆን እውነቱን ተናግረው እመሸበት የሚያድሩ እውነተኛ የቀለም ልጆች መኖራቸውን አሌ የምንል አይመስለኝም። ያመኑበትን ተናግረው የለት እንጀራቸውን ያጡ ግን ደግሞ የቀለም ቃልኪዳናቸውን የጠበቁ ጀግና ምሁራን መኖራቸውን ዋቢ ጠቅሶ መከራከር ይቻላል። ሌላው ቢቀር የባለጊዜ ፖለቲከኞች ቃለአቀባይ በመሆን ሳይማር ባስተማረን ወገን ላይ ባላስተማረን ትምህርት በሃሰት ከምንፈርድ እሰየው ባያሰኝም እንኳን ጎመን በጤና ያሉትን ጎራ መቀላቀል ሳይሻል ይቀራል። ለነገሩ እሱም መፈቀዱ እርግጠኛ መሆን አይቻልም።

አንድ በንጉሱ ዘመን ሹመት የተሰጠው ሰው ሹመቱን አልፈለገው ኖሮ ንጉሱ ፊት ቀረበና እባክዎ ጃንሆይ፣ ሹመቱ ቀርቶብኝ አርሼ ልብላበት ቢላቸው፥ አይ ሞኝ፣ እሱንስ እኛ ስንፈቅድ አይደል? አሉት ይባላል። እውነት ይሁን አይሁን አላውቅም ግን ተናግሮም ሆነ ዝም ብሎ መኖር በዛሬይቱ ኢትዮጵያ እንዲህ ቀላል ምርጫ እንዳልሆነ እረዳለሁ። እናም ዝም ብሎ ከመጠቃት ዋሽቶ መጠቀም የሚል ፈታኝ እና ጨካኝ አቋም የሚወስዱ ምሁራን ቢኖሩ ልንፈርድባቸው አይገባም ካላችሁ ባላምንበትም ልስማማ እችላለሁ። ብቻ ቁም ነገሩ ሀሰት ተናግረው የተጠቀሙትም፣ ፈርተው ዝም ያሉትም መባከናቸው ነው።

ኢትዮጵያ ከሁለቱም አላተረፈችም። ሁሉንም አጥታለች።

ኢትዮጵያ እግዜር ያፅናሽ! አሜን?


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule