• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አንድ ህዝብ አንድ ሀገር!

July 29, 2016 03:15 am by Editor 2 Comments

ሰው ነፃነት ይፈልጋል። ነፃነት ላለመፈለግ ራሱ ነፃነት ይጠይቃል። ስለዚህ ነፃነቱን የሚቃወም አይኖርም። ምክንያቱም ነፃነትን በራስ መቃወም በራሱ ነፃነት ነው። ሰው ነፃ ለመሆንም ላለመሆንም ነፃ መሆን አለበት። ሰው ነፃ ላለመሆን የመወሰን ነፃነት አለው። ዋናው ጉዳይ ዉሳኔው የራስ መሆን አለበት፤ የሌላ አካል ጣልቃ ገብነት ሊኖረው አይገባም።

ነፃነት የሰው ነው፤ የራሳችን ሃብት ነው። በሌሎች ጣልቃ ገብነት ሊገደብ ግን ይችላል። ስለዚህ ነፃነታትችን ከፈለግን መጠበቅ ይኖርብናል። ነፃነታችንን ለመጠበቅ ፈፃሚ ተቋም ያስፈልጋል። ፈፃሚ ተቋም ወይ ስርዓት የሚኖረው መንግስት ሲኖር ነው። መንግስት የሚኖረው ሀገር ሲኖር ነው። ሀገር የሚኖረው ህዝብ ሲኖር ነው።

የምንፈልገው ነፃ ህዝብ ነው። ነፃ ህዝብ የሚኖረው ዴሞክራሲያዊ መንግስት ሲኖር ነው። ዴሞክራሲያዊ መንግስት የሚኖረው የዴሞክራሲ ግንዛቤ ያለው ህዝብ ሲኖር ነው። ግንዛቤ ያለው ህዝብ መብቱ ያውቃል፤ መንግስት አገልጋይ እንጂ ጌታ አለመሆኑ ይረዳል።

ባጠቃላይ ህዝብ የስልጣን ባለቤት ሲሆን ዴሞክራሲያዊ መንግስት ይኖራል። እናም ነፃነቱን ያረጋግጣል። ህዝብ የስልጣን ባለቤት የሚሆነው መንግስትን መቆጣጠር ሲችል ነው። መንግስትን መቆጣጠር ስልጣን መስጠትንና መንጠቅን ይጨምራል።

ህዝብ መንግስትን መቆጣጠር የሚያስችል ዓቅም የሚፈጥረው አንድነት ሲኖረው ነው። ሰለማዊ ህዝብ በጎሳ፣ በቋንቋ፣ በሀይማኖት፣ በአከባቢ ወዘተ ሳይከፋፈል በአንድነት ሲቆም መንግስትን ይቆጣጠራል። በአንድነት መቆም ማለት የግድ አንድ ዓይነት የፖለቲካ ኣቋም መያዝ አይደለም። የራሱ የመሰለውን አመለካከት ይኖረዋል። የሚወሰነውም በአብዛሃ (አብላጫ) ድምፅ ነው። ምክንያቱም ሁሉም ሰው ነፃ ነው።

ስለዚህ ነፃ ህዝብ እንዲኖረን ነፃ መንግስት ያስፈልጋል። ነፃ መንግስት እንዲኖረን የህዝቦች አንድነት ያስፈልገናል። የህዝቦች አንድነት እንዲኖር የሀገር አንድነት መኖር አለበት። ምክንያቱም የሀገር አንድነት ከሌለ የህዝብ አንድነት አይኖርም። የህዝብ አንድነት ከሌለ የህዝብ ስልጣን አይኖርም። የህዝብ ስልጣን ከሌለ ዴሞክራሲ አይኖርም። ዴሞክራሲ ከሌለ ነፃነት አይኖርም። ነፃነት ከሌለ እኩልነት አይኖርም። እኩልነት ከሌለ ፍትሕ አይኖርም። ፍትሕ ከሌለ የህዝቦች አንድነት አይኖርም። የህዝቦች አንድነት ከሌለ የእርስበርስ ችግር ይኖራል። የእርስበርስ ችግር ሀገርን ያፈርሳል። ሀገር ከፈረሰ ምንም አይኖርም።

ስለዚህ ነፃነት ከፈለግን ሀገር ያስፈልገናል። ሀገር ከፈለግን አንድ ህዝብ (የሚተባበር ህዝብ) ያስፈልገናል። አንድ ህዝብ ከፈለግን ነፃነት ያለው መሆን አለበት። ነፃነት የሌለው ህዝብ ወይ ሀገር አይቆምም። ስለዚህ ሀገር እንዲቆም ነፃነት ያስፈልጋል። ነፃነት እንዲከበር አንድ ሀገር፣ አንድ ህዝብ አስፈላጊ ነው።

ጨቋኝ ገዢዎች ግን የህዝቦችን አንድነት አይፈልጉም። ምክንያቱም ህዝብ አንድ ከሆነ፣ ከተባበረ ከስልጣን ያስወግዳቸዋል። ለዚህም ነው ብዙ ግዜ “የከፋፍለህ ግዛ” ስትራተጂ የሚጠቀሙ። ስለዚህ ነፃነት ፈላጊዎች እንዲያሸንፉና የህዝብና የሀገር አንድነት እንዲጠብቁ የህዝቦችን አንድነት አደጋ ላይ የሚጥል ተግባር አንስራ። መከፋፈል ለገዢዎች ይጠቅማል።

አዎ! አንድ ህዝብ አንድ ሀገር ለነፃነት።

It is so!!!

(ምንጭ: መረጃ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. gud says

    July 30, 2016 02:58 pm at 2:58 pm

    Excellent and meticulous job of EPRDF has exposed One country advocates as Narrow
    racists .

    One country one people mask unveiled .
    Viva nation nationalities . Amhara is just one gosa in the equation .

    Reply
  2. koster says

    July 31, 2016 07:41 am at 7:41 am

    As long as the fascists from TIGRAI are not dismantelled, our dream of freedom and equality will be in vain. So we should unite to dismantle these home grown fascists. TPLF fascists made the politics very complicated but if we unite all could be solved. The 23 years of the fascists experiment of ethnic federalism/ethnic cleansing is a failure. The forcefully taken land from Gondar, Wollo, Afar and the land grabbing of TPLF fascists should be stopped.The federalism and the constitution made by TPLF and OLF which excluded one of the major ethnic group – Amharas is not binding and should be dismantelled with the fascists. We are not barbaric like the fascists to evict the Tigrians settled on Amhara and Afar land but the ethnic federalism should be dismantelled so that all Ethiopians can live whereever they want. No greater Tigrai, the pre-1991 Ethiopian map should be restored and then the administrative regions will be reorganized again by a free and democratic parliament. There will be two or more national/official languages so that citizens living in one country understand each other.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule