• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሁለት ላሞች/የስርዓተ ማህበሮች ትርጓሜ

September 20, 2014 01:53 am by Editor 1 Comment

የየዘመኑን ስርዓተ ማህበር ምንነት ቅልጥጥ አድርጎ ለማሳየትና የማያሻማ ፍቺ ለመስጠት የየሀገሩ የቱርጁማን ጠበብት ያልቧጠጡት የሃሳብ ኮረኮንችና ያልዳሰሱት ሸካራ ብሂል የለም፡፡ በየዘመኑ ለተከሰቱ የማህበረሰብ አስተሳሰቦች ከተለያዩ ምሁራን የተለያየ ፍቺና ትርጓሜ ተሰጥቷል፡፡ ምሁራኑ በዘመናችን ከደረሱበት መተርጉም አንዱ በሁለት ላሞች ተምሳሌትነት የቀረበው ነው፡፡ የነጠረውን ፍጹማዊ መተርጉም እስኪያገኙ ድረስ የፈረንጅ ሊቃውንት ይህንን በሁለት ላሞች ላይ የተመሰረተ ተምሳሌታዊ መተርጉም ሰጥተዋልና ከግልዎ ግምገማ ጋር በማያያዝ ይህችን አጭር ሐተታ ያነጻጽሩት ዘንድ እነሆ ብለናል፡፡

1. ሶሻሊዝም

እርስዎ ሁለት ላሞች ይኖርዎታል እንበል፡፡ በሶሻሊዝም ስርዓተ-ህይወት እስካሉ ድረስ አንዲቷን ላም ለራስዎ መድበው ሌላይቱን ለጎረቤትዎ መዳረግ ግዴታዎ ነው፡፡

2. ኮሚኒዝም

እርስዎ ሁለት ላሞች ይኖርዎታል እንበል፡፡ በኮሚኒዝም ስርዓተ ማህበር ውስጥ እስካሉ ድረስ መንግሥታዊው የኮሚኒስት ፓርቲ ሁለቱንም ላሞችዎን ይወስድብዎትና የድርሻዎ ያህል ብቻ ወተት ያድልዎታል፡፡

3. ፋሺዝም

እርስዎ መንታ ላሞች አሉዎት እንበል፡፡ በፋሺዝም ስርዓ-ህይወት እስካሉ ድረስ የሚገዛዎ የመንግሥት ቁንጮ ሁለቱንም ላሞችዎን ይነጥቅና የሚያልበውን ወተት ለራስዎ ይሸጥልዎታል፡፡

4. ናዚዝም

እርስዎ መንታ ላሞች አሉዎት እንበል፡፡ በናዚዝም ስርዓተ-ሕይወት እስካሉ ድረስ ጨካኙ መንግስት ሁለቱንም ላሞችዎን ዘርፎ ከወሰዳቸው በኋላ ራስዎን ጭምር ያርድዎታል፡፡

5. ቢሮክራሲዝም

እርስዎ ጥንድ ላሞች አሉዎት እንበል፡፡ የሚኖሩበት ስርዓተ ማህበር ቢሮክራሲዝም እስከሆነ ድረስ ሁለቱንም ላሞች ይወስድብዎትና አንደኛይቱን ያርዳታል፤ ሌላይቱን ግን እያለበ ወተቷን እመቅ ያፈሰዋል፡፡

6. ካፒታሊዝም

እርስዎ የሁለት ላሞች ባለቤት ነዎት እንበል፡፡ የሚኖሩበት ስርዓተ ማህበር ካፒታሊዝም እስከሆነ ድረስ በዘዴ ይወስድብዎና አንዲቷን ላም ከሸጠ በኋላ ለገዛ ራሱ ለማራባት ሲል በተሸጠችው ላም ገንዘብ ኮርማ ይገዘባበታል፡፡

ማን ቀረ? ማኦይዝም፤… ሌኒንዘም፣ . .. ራዲካሊዝም፣… ሊብራሊዝም፣ ኒኦ-ሊብራሊዝም፣ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ወዘተ… አሉ፡፡ እስቲ በዚህ የሁለት ላሞች ቀመር መሰረት ራስዎ የሚኖሩበትን ስርዓተ ማህበር ለመተርጎም ይሞክሩ፡፡
*****
(ሀይሉ ገብረዮሐንስ፣ ኢትኦጵ መጽሔት፣ ቅጽ 3፣ ቁጥር 031፣ ታህሳስ 1994፣ ገጽ 4)
*****
በጉዳዩ ላይ ድረገጾችን ስንመለከት ያገኘነውን አንድ እኛ እንጨምር:-

7. የቻይና ዓይነት ኮሙኒዝም

እርስዎ መንታ ላሞች አሉዎት እንበል፡፡ እነዚህ ሁለት ላሞች በ300 ሰዎች ይታለባሉ:: ስርዓተ ማህበሩ ባገር ሁሉ ሥራዓጥነት በጭራሽ የለም፣ ምርታማነት አድጓል፣ ተመንድጓል፣ ህዳሴ፣ ውዳሴ ነው ይላል:: እውነት የሚዘግበውን ጋዜጠኛ ይረሸናል፡፡
—–
ጽሁፉን ያገኘነው ከAfendi Muteki ፌስቡክ ገጽ ነው፡፡

Afendi Muteki is a researcher and author of ethnography and history with special focus on the peoples of East Ethiopia. You may follow him on his facebook page. Just click here.

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. wondimu bialifew says

    September 20, 2014 09:34 am at 9:34 am

    greater

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule