• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በህወሓት ተወርረናል!” ደቡብ ሱዳኖች

January 11, 2013 07:55 am by Editor 6 Comments

አዲሷ አገር ደቡብ ሱዳን እንደ መንግሥት ተመቻችታ አልቆመችም። የፋይናንስ ስርዓቱም የተረጋጋ አይደለም። የገቢና ወጪ ቁጥጥሩ ክፍተት ያለበት በመሆኑ ለሙስና የተጋለጠ ነው። የጁባ ነዋሪዎች እንደሚሉት ከሆነ የአገሪቱ ሃብት በግለሰቦች እጅ ነው። በተለያዩ መስኮችም የባለሙያና የአቅም ችግር አገሪቱ ምስጢርና የኔ የምትለው አስተዳደር እንዳይኖራት አድርጓታል የሚሉ በርከቶች ናቸው።

ይህንኑ ክፍተት ለመሙላት በሚል ኢህአዴግ ደቡብ ሱዳንን ከተወዳጀ ጀምሮ ከፍተኛ ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል። የመከላከያ መኮንኖችን አሰልጥኗል፤ የፖሊስ ኃይሉን አደራጅቷል። በአማካሪነት በተለያዩ ዘርፎች የራሱን ሰዎች ጠቅጥቆ አሁንም ይህንኑ ድጋፉን አጠናክሮ ቀጥሏል። የተመሰረተው ግንኙነት ወደፊትም እንዲሁ በቀላሉ ንፋስ የሚገባው አይመስልም። ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው እንደሚሉት ኢህአዴግ በህወሃት አማካይነት ደቡብ ሱዳንን ጠፍንጎ የያዘበት ሰንሰለት በቀላሉ ሊበጠስና ሊሸረሸር የሚችል እንዳልሆነ ይናገራሉ።

ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ እነዚሁ በጁባ የሚኖሩ ክፍሎች በፋይናንስ፣ በፖሊስ፣ በመከላከያ፣ በደህንነት፣ በተለያዩ ከፍተኛ ግዢዎችና በገንዘብ ዝውውር በኩል የደቡብ ሱዳን ማናቸውም እንቅስቃሴ ከኢህአዴግ እይታና ክትትል ውጪ አይደለም። እንደ አገር ኢትዮጵያ በቀጠናው ኃያል መሆኗ ቢያስደስትም አሰራሩ “ህወሃት በኢትዮጵያ ስም፣ የህወሃት ልጆች በኢህአዴግ ስም” መከናወኑ ቅሬታ ፈጥሯል።

“ብሔራዊ ጥቅምን በብሔራዊ አጀንዳ ማስጠበቅና ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ማስኬድ ኩራቱ የሁሉም ዜጎች እንዲሆን ያደርገዋል” የሚሉት ክፍሎች በተግባር የሚታየውና በብሔራዊ ስም የሚከናወነው ስራ “ህወሃትና የህወሃት ሰዎች በብቸኛነት እንዲጠቀሙበት የሚያደርግ ነው፤ ሕዝብ የወከለውና የራሱን አገር ጥቅም የሚያስከብር አስተዳደር በኢትዮጵያ ላይ እስከለሌለ ድረስ አካሄዱን ብሔራዊ ወይም የአገር ኩራት ለማለት አይቻልም” ብለዋል። አያይዘውም ኃያልነታችን በብሔራዊ ደረጃ እንጂ በድርጅትና በጎሣ ደረጃ መሆን የለበትም በማለት ይከራከራሉ፡፡ ሲያስረዱም በብሔራዊ ሽፋን ለመበልጸግ የሚደረግ ሩጫ ዓቅምን ካላገናዘበው የኤርትራ ፍላጎትና በውጤቱም ከጎረቤት ሁሉ ጋር ከጠብ እስከ ዓይነቁራኛ መተያየት ከመድረስ ጋር ልዩነት አይኖረውም ይላሉ፡፡

በአቅም ማጎልበት፣ በማማከርና በባለሙያ ድጋፍ ስም የሚካሄደው ምልመላና ምደባ በቀጥታ ተቀማጭነቱ ጁባ ከሆነው የመረጃና የደህንነት ቡድን ጋር የሚቆራኝ ነው። በምልመላው የሚካተቱት አብዛኞቹም ከህወሃት የሚወከሉ ናቸው። ከዚሁ የመረጃ ቡድን ጋር በመተሳሰር የሚሰሩ ነጋዴዎችና በግል ስራ የሚንቀሳቀሱ የትግራይ ተወላጆችም አሉበት።

በብሄራዊ ደረጃ በጥንቃቄ መያዝ ያለበት የጥቅም፣ የኢኮኖሚ ስትራቴጂና የደህንነት ጉዳይ በፓርላማውም ሆነ በአባል የኢህአዴግ ድርጅቶች በወጉ የማይታወቅ፣ በዚሁ ሰንሰለት ስር የሚገኘው ያገሪቱ ገቢ ቁጥጥር የማይደረግበት እንደሆነ የመረጃው ምንጮች ይናገራሉ። አያይዘውም ይህንኑ ብሔራዊ ሽፋን ያለውን ግንኙነት በመንተራስ የህወሃት ሰዎች አለአግባብ እየበለጸጉበት መሆኑን አመልክተዋል።

በደቡብ ሱዳን የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት ከሚሰጡት 5ኩባንያዎች አንዱ የሆነው Vivacell 30ኢትዮጵያውያንን በቴክኒክና ፋይናንስ መስክ ቀጥሯል:: (ፎቶ: አዲስ ፎርቹን)

የሚሰሩበትን አገርና ስማቸውን እንዳይገለጽ የጠየቁ በሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ የተማሩ የደቡብ ሱዳን መንግስት የመዋቅር ሰው “ህወሃት ወርሮናል” ሲሉ አስተያየታቸውን ይሰጣሉ፤ “ከተራ የችርቻሮ ንግድ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ የወጪና የገቢ ንግድ የህወሃት ሰዎች እየተቀራመቱን ነው” የሚሉት እኚሁ ሰው በከፍተኛ ደረጃ ባሉ አመራሮች ዘንድ የሚሰማው ቅሬታ እየጨመረ መሆኑንን ያስረዳሉ።

“አገራችን” አሉ “አገራችን ካንዱ ነጻ ከወጣች በኋላ ሌላ እጅ ላይ የወደቀች ያህል የሚሰማን ብዙዎች ነን” በማለት ቅሬታቸው የጨመረ ክፍሎች መበራከታቸውን የሚናገሩት የደቡብ ሱዳን ከፍተኛ ሰው፣ በትግሉ ዘመን ኢትዮጵያ ያደረገችው ድጋፍ የሚረሳ ባይሆንም አሁን እየተደረገ ያለው ድርጊት ከብሔራዊ ደረጃ የወረደ ስግብግብነት፣ ለመዝረፍ የመራወጥ፣ በከፍተኛ ደረጃ ደግሞ ሙሉ የአገሪቱን ንግድ እንቅስቃሴ የመቆጣጠር እንደሚመስላቸው አመልክተዋል።

“በበርካታ ባልደረቦቼ ዘንድ ያለው እምነት እንደገና የመወረር ዓይነት ነው” በማለት አስተያየታቸውን የሚያጠናክሩት ባለስልጣን፣ ውስጥ ውስጡን ያለው ቅሬታ ሳይባባስ ኢህአዴግ ከደቡብ ሱዳን ጋር ያለውን ግንኙነት “ክብር የተላበሰ፣ በአገርና በመሪዎች ደረጃ ስትራቴጂና የጋራ ጥቅም ላይ ብቻ ባተኮረ መንገድ ለማድረግ አካሄዱን መመርመር አለበት” ባይ ናቸው።

“ካለብን ተጽዕኖ የተነሳ ለባለውለታችን ፕሬዚዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም ያሰራነውን ቪላ ለመሸለም እንኳን አልቻልንም” ሲሉ የተጠፈሩበትን የቁጥጥር ገመድ ጥብቅነት ባለስልጣኑ አመልክተዋል። አያይዘውም ይህ ስሜት እያደገ ሲመጣ ህወሓት አገር ውስጥ ከሚታማበት የንግድ የበላይነት ጋር ተዳምሮ አላስፈላጊ መተራመስ ሊያስከትል ይችላል የሚል ስጋት እንዳላቸው ተናግረዋል። ደቡብ ሱዳን ነጻ አገር መሆኗን ስታውጅ ባለስልጣናቱ በዕለቱ ለኮሎኔል መንግስቱ ቪላ ቤት ለመሸለም እቅድ መያዛቸውን ይፋ ማድረጋቸው፣ እቅዱ በተለያዩ ሚዲያዎች ይፋ እንደሆነ የኢህአዴግ የስለላ ሰዎች ባደረጉት ተጽዕኖ እቅዱ መሰረዙንና ቀደም ሲልም የተነገረው ስህተት መሆኑ ተጠቅሶ ማስተባቢያ መበተኑ የሚታወስ ነው።

ጄኔራል ጻድቃን በበላይነት የደቡብ ሱዳን የመከላከያና የደኅንነት አማካሪ እንደሆኑ በማስታወስ አስተያየት የሚሰጡት ክፍሎች፣ ህወሓት በኢትዮጵያ እንዳደረገው በደቡብ ሱዳንም ለወደፊቱ ታላቅ የንግድ ኢምፓየር ለመክፈት ዝግጅት እንዳለ ገልጸዋል። እነዚህ ክፍሎች እንደሚሉት ኢህአዴግ ብሔራዊ ክብሩን ጠብቆና ብሔራዊ ኃላፊነቱን በማስቀደም ካልተንቀሳቀሰ በውስጥም በውጪም ችግር ይገጥመዋል።

በደቡብ ሱዳን የሚፈጸሙ በርካታ ጉዳዮች ቢኖሩም ሙሉ በሙሉ ዝርዝሩን ለጊዜው ከመናገር መቆጠባቸውን የሚናገሩት ወገኖች “ኬንያን ጨምሮ በቀጣናው ኃያል አገር መሆናችን ያስደስተናል። ይህ የኃያልነት ሚናችን እንዲቀጥል በብሔራዊነት ስር ሃብት እያግበሰበሱ ያሉትን ወገኖች መለየትና፣ መንግሥትም እንደ መንግሥት ክብሩን ሊጠብቅ ይገባል” በማለት ማሳሰቢያቸውን ያስተላልፋሉ። ከሌሎቹ ከባድ ንግዶች ውጪ ህዝብ እየተራበ በኮንትሮባንድ እህል ወደ ሱዳንና ወደ ሌላም አገር የሚያጓጉዙት ክፍሎች፣ በሱዳን በባለሃብት ስም የሚንቀሳቀሱትንና በተራ የሱቅ በደረቴ ስራ ተሰማርተው ዶላር የሚሰበስቡት ክፍሎች ጉዳይ ሊታሰብበት እንደሚገባም አሳስበዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. dubale says

    January 11, 2013 01:40 pm at 1:40 pm

    fantasy world!!…u can create article out of blue

    Reply
    • ሰንጢው says

      January 11, 2013 06:57 pm at 6:57 pm

      ማነው ያልከው ስምህን? ዱባለ? ውነት ነው እንደስምህ ዜናም ዱብ የሚል ይመስልሃል! “ዱባለ” አሉህ እንጂ ከመረገዝህ በፊት ስንት መከራ ጭንቀትና ሃይል ወጥቶ ከዚያም እስክትወለድ ወራት ተቆጥሮ … እንጂ እንደው እንደ ሾላ ፍሬ ዱብ አላልክም:: ግን በጣም በስምህ ወይም ስምህን በሚመስል የአስተሳሰብ ባህርይ አማኝ ስለሆንክ ያልተስማማህን ነገር “ዱባለ” ትለዋለህ:: አይፍረድብህም:: ግን ዱብ የማይሉ ብዙ ነገሮች አሉ:: ዜናው ለኔ በጣም ጥንቃቄ የተሞላበትና መግለጽ ከሚገባው በላይ ብዙ ጉዳዮችን ያልገለጸ ነው የሚመስለኝ – ከጎልጉል አዘጋጆች ጸባይና ባለሙያነት አንጻር ስመለከተው ብዙ እያወቁ በጣም ጥቂቱን ብቻ ለዜና ፍጆታ የተጠቀሙበት ይመስለኛል::
      ስማ ዱባለ – አይበቃህም!?
      ሰንጢው ነኝ ከጁባ

      Reply
  2. Nuer Land says

    January 11, 2013 07:21 pm at 7:21 pm

    Ethiopia and South Sudan are brothers and sisters. Ethiopia can’t live without South Sudan and South Sudan can’t live without Ethiopia. During the Ethiopia war with Italian. People of South Sudan intervene to helf big sister. For smart, and tactic people of South had, they led Big sister to defeat Italian colonization and that is fact

    Reply
  3. Charles okoth says

    January 12, 2013 12:11 am at 12:11 am

    Mengistu former president of Ethiopian was NOT been on seat those years 4 ever but he’s over thrown from the power, so I mean that EPDRF especially T P L F Will not be longer there 4 ever & we’ll not forget it till God say . Melse zenawi dead & i do believed many others will follow him. SUDAN 21 years in war & they were forgotten ok,well God bless them

    Reply
  4. ዱባለ says

    January 13, 2013 12:33 am at 12:33 am

    Please note that dubale and ዱባለ are not the same person.

    Reply
  5. Jobii says

    January 18, 2013 10:16 pm at 10:16 pm

    It is true. But frankly saying, Eritreans are almost the ‘sole’ riders of South Sudan economy. Poor South Sudan.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule