• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምርጫ፦ ህወሃት ወይስ ግብጽ?

June 8, 2013 01:48 am by Editor Leave a Comment

አቶ መለስ ዜናዊ የአባይ ግድብን ለመገንባት መስተዳደራቸው መቼ እንደወሰነ ሲጠየቁ ውሳኔው ከ2002 ዓ.ም. በኋላ እንደሆነ ተናግረው ነበር። አቶ መለስ በአንጎላቸው ውስጥ የነቀርሳ ዕጢ እንዳለባቸው ያወቁት ከ2002 ዓ.ም. በፊት ነው።

እንግዲህ የቀድሞው ጠሚራችን (ጠቅላይ ሚኒስትራችን) አባይን ለመገንባት ለምን እንደተመኙ ስጠራጠር ምናልባት የሳቸው መስተዳደር የፈጠረውን አገራዊ መከፋፈል እና የራሳቸውን ታሪካዊ ትሩፋት (legacy) ለማግነንና ለመቤዤት ጭምር ሳይሆን አይቀርም።

የቀድሞው ጠሚራችን ህመማቸው እንደሚገላቸው ያዉቁ ነበር ቢባል ማጋነን አይመስለኝም። አቶ መለስ ታሪክ በበጎ አይን እንዲያያቸው አባይን መገደቡን ጥሩ አማራጭ አርገው አግኝተውታል።

አባይ የሚገደበው በአማራ ክልል ውስጥ አይደለም ፤ በቤንሻንጉል እንጂ። አባይ የኢትዮጵያውያን መንፈስን በቁጪት ጠፍሮ ያሰረ ወንዝ ነው። አባይን መገደብ ለአቶ መለስ ኢትዮጵያውያንን ለማስተሳሰር ትልቅ አጋጣሚ ሆኖላቸዋል። የቀድሞው ጠሚር “አባይን ደፈረ” መባሉን ከዚህ አለም ከመለየታቸው በፊት መስማታቸው የህሊና እረፍት ሰቷቸው ይሆናል።

ሰሞኑን የግብጽ ፓለቲከኞች ሲዶልቱት የነበረውን ቅዠት ሰምተው “ወያኔን ከግብጽ ጋር ተባብረን እንደመስሰዋለን” ሲሉ የተሰሙ ወገኖች አሉ። ግብጽ የአባይን ግድብ በቦንብ ለመደበድብ የሱዳንን አየር መጠቀም የግድ ነው። ሱዳን ከመቼውም የበለጠ የተናጋ ሁኔታ ላይ ያለች አገር ናት። ለሁለት ተከፍላለች ፡ ዳርፉሮች መገንጠል ይፈልጋሉ ፤ ስለዚህ ከኢትዮጵያ ጋር በሰላም መኖር ለሱዳን የግድ ነው።

ሱዳን ከግብጽ ጋር ነው ምሰራው ብላ ሰማይዋን ለግብጽ ጦር አዉሮፕላን ብትከፍት ፡ ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ፡ ከዳርፉር አማጽያን ፡ ከሱዳን ተቃዋሚዎች ጋር ፡ እንዲሁም ከምዕራቡ አለም ጋር በመተባበር የሱዳንን ፓለቲካ መናድ የምትችልበት ሁኔታ ሰፊ ነው።

ግብጽ እንደምንም ብላ ግድባችንን በቦንብ ብትደበድብ ኢትዮጵያ የግብጽን ትልቅ ግድብ (አስዋን ግድብ) እንደምንም ብላ በቦንም የመደብደብ አማራጯን መጠቀሟ አይቀርም።

ግብጾች የአባይን ግድብ እንኳንስ በቦምብ ዝንቡንም እሽ የማለት ድፍረት የላቸውም። እንዲያውም የግብጽ ባለሃብቶች ኢትዮጵያ ውስጥ ሰፋፊ የስንዴ እርሻ መከራየታቸው አይቀርም። ኢትዮጵያም ለግብጽ ትልቅ የሰብል ንግድ አጋር እንደምትሆን ግብጾች ያቃሉ ፡ ያንንም አማራጭ ለመጠቀምም ተዘጋጅተዋል።

ታዲያ ይሄ ሁሉ ተጨባጭ ሁኔታ እያለ ፡ ምነው አንዳንድ የዲያስፓራ ወገኖች “ከህወሃት ይልቅ ግብጽ ይሻለናል” የሚል ጸያፍ የአገራዊ ጥቅምና ህልውናን አሳልፎ የሚሰጥ አቋም እንወስዳለን?

ግን ይሄ ሁሉ ግር-ግር የሰማያዊ ፓርቲን ትልቅ ሰላማዊ ሰልፍ እንዴት ከመቅጽፈት አስረሳን? ዲያስፓራ ምራቁን ያልዋጠ ፡ በወሬ በቀላሉ የሚረታ ፡ ስሜቱ የሚቀድመው ፡ ሆድ የባሰው ማህበረሰብ መሆኑ ባለፉት 22 ዓመታት አንድ እርምጃ መራመድ ያልቻለ ማህበረሰብ ለመሆኑ ጠቋሚ ነው።

የአባይ ግድብ ይገደባል። ግድቡን የገነባው ይገንባው ፡ ግን ይገደባል።

የዴሞክራሲ ፡ የፍትህና የዜጎች ህገመንግስታዊ መብቶች መከበር ትግልም ይጧጧፋል። ከሰማያዊ ፓርቲ ጅማሬ ጋር ወደፊት!

—————————————————————————————————————

አስተያየትና ትቺቶችን በዚህ ይላኩልኝ፦ yared_to_the_point@yahoo.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule