• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሕዝባዊው ንቅናቄ ኢህአዴግ ሠግቷል

December 12, 2015 11:25 am by Editor 1 Comment

ለጎልጉል የእማኝ ዘጋቢ (ireporter) የሆኑ በላኩልን መረጃ መሠረት በኢትዮጵያ የተለያዩ ቦታዎች የተነሣው ንቅናቄ ወደ ሲቪል ሠራተኞች ዘልቆ እንዳይገባ ስጋት ውስጥ የገባው ኢህአዴግ ሠራተኞችን ማባበልና ማንቃት ጀምሯል፡፡

በተያዘው ዕቅድ መሠረት በአዲስ አበባ በሚገኙ ወረዳዎች ውስጥ በሲቪል ሠራተኝነት የሚታወቁ ዜጎችን ኢህአዴግ በየቦታው መሰብሰብ ጀምሯል፡፡ እማኙ በላኩት መረጃ እንደገለጹት ለሁለት ቀን በሚካሄደው ስብሰባ በየወረዳው ለሚሰበሰቡ ሠራተኞች ቢያንስ ብር 300 አበል በመስጠት የማባበያ ስብሰባው እንደሚካሄድ ገልጸዋል፡፡ በየወረዳው ካለው ሲቪል ሠራተኛ አንጻር ለአበል የታሰበው ብር በሚሊዮን ሊቆጠር እንደሚችል እማኙ ጨምረው አስረድተዋል፡፡

ዋናው አጀንዳ ሲቪል ሠራተኛው እየተካሄደ ባለው ንቅናቄ ተሳታፊ እንዳይሆን፤ እንዳይተባበር፤ ድጋፍ እንዳይሰጥ፤ … ሲሆን ተሰብሳቢዎቹ ወደ ስብሰባው የመጡት የህወሃት/ኢህአዴግ ደጋፊ ሆነው ሳይሆን አለመሳተፍ የሚያመጣባቸውን ከመፍራትና በነጻ ስለሚያገኙት አበል በማሰብ እንደሆነ እማኝ ዘጋቢው ጨምረው ገልጸዋል፡፡ ሰብሳቢዎቹ “ንቅናቄውን እንዳትደግፉ” ወይም “ማስተር ፕላኑን በተመለከተ የተነሳውን የኦሮሞ ተቃውሞ እንዳትደግፉ” ወይም መሰል ግልጽ ማስጠንቀቂያ ለተሰብሳቢዎቹ እንዳልሰጡ መረጃውን የላኩት እማኝ ዘጋቢ ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ይልቅ ግን በተዘዋዋሪ ሁኔታ ከጸረ ልማት ኃይሎች ጋር እንዳትተባበሩ፤ ጸረ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎችን እንዳትደግፉ፤ ተገልጋዩን ኅብረተሰብ በጥሩ ያዙ፤ የገቢ ግብር ይቀነሳል፤ … የሚሉ ማባበያና ማስጠንቀቂያ አዘል ንግግሮች ከሰብሳቢዎቹ እንደተደመጡ ዘጋቢው አስረድተዋል፡፡

ይህ በግምገማ ሽፋን የሚካሄደውን የሲቪል ሠራተኞች ስብሰባ ከሌላ ነጻ ምንጭ ለማረጋገጥ ባይቻልም እማኝ ዘጋቢው በላኩልን መረጃ መሠረት ስብሰባው በይፋ እንዳይታወቅ መፈለጉንና ከወረዳ ጽ/ቤቶች ውጪ በሚገኙ ቦታዎች መካሄዳቸውና በዚሁ እንደሚቀጥል አክለው ተናግረዋል፡፡

በአዲስ አበባ ዙሪያ የታቀደውን ማስተር ፕላን በመቃወም በተማሪዎች የተነሳው ተቃውሞ በአገሪቱ የተለያዩ ቦታዎች በመቀጠሉ ከተማሪዎች አልፎ ነዋሪዎች እየተቀላቀሉት እንደሆነ በስፋት ይነገራል፡፡ በማኅበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩት መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በንቅናቄው ምክንያት እስከ 25 ሰዎች መገደላቸው ተዘግቧል፡፡ ከሞቱት መካከል ከአስር ዓመት በታች የሚሆኑ እንዳሉበት የተነገረ ሲሆን በምዕራብ ሸዋ ነዋሪዎች አንዳንድ ከተሞችን በራሳቸው ቁጥጥር ሥር ማዋላቸው ሲነገር ይህንኑ መረጃ አፍቃሪ ህወሃት/ኢህአዴግ የሆኑ የሥርዓቱ ቀጥተኛ ተጠቃሚዎች፣ ተላላኪዎች፣ አሽቃባጮችና ጭፍን ደጋፊዎች በየፊናቸው አረጋግጠዋል፡፡

ሕዝባዊ ንቅናቄውን የኦሮሞ ብቻ አድርጎ መውሰድና በዚያ መልኩ ፕሮፓጋንዳ መስጠት በኢትዮጵያ ውስጥ በህወሃት ሲረጭ የኖረውን የዘር ጥላቻና መከፋፈል የከፋ ደረጃ ላይ አድርሶ ራስን ለህወሃት መጠቀሚያነት የሚያጋልጥ የሚናገሩ ወገኖች “ኦሮሚያን” እንደ አገር እያሰቡና ሠንደቅ እየያዙ መውጣት በንቅናቄው ላይ ሊጠገን የማይችል አሉታዊ ተጽዕኖ ያመጣል ሲሉ ስጋታችን ይገልጻሉ፡፡ (ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Jaawii says

    December 15, 2015 11:01 pm at 11:01 pm

    Hallo Gulgoole,
    Good that your covering the current situation in Ethiopia and express the overall fear of a risk that the country is going to face. BUT as media outlet be careful with a message you are passing. Yes, the Oromoo people is right now fiercely raising its voice and being killed day and night by brutal government heavy armed forces. Unless others join the Oromoo to make it a national popular uprising, how can you claim it will be a national uprising. You can not stand passive and say criticize by saying “Oromoo is fighting for itself’. The Oromoo people did not say we are fighting for an oromoo nation alone; they say we are fighting for our right. Do not mess up things, please !! You need to give a message that encourage all other oppressed people to genuinely and immediately act in supporting the Oromoo people.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule