• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ነጻ አውጪ ግምባር አገዛዝ እንጂ መንግሥት አይመሠርትም

October 9, 2015 08:12 am by Editor 1 Comment

ላለፉት 25 ዓመታት በነጻ አውጪ ግምባር ስም ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር “ኢህአዴግ” ብሎ በፈጠረው ስያሜ አገር በግፍ እየገዛ መሆኑ ሳያንስ በየአምስት አመቱ በሚያካሂደው “ምርጫ” የሚመሠርተው “መንግሥት” መፍትሔ ሊሰጥ እንደማይችል መድረክ አስታወቀ። ሰማያዊ ፓርቲ በበኩሉ በኢትዮጵያ ለተከሰተው ረሃብ የአገዛዙ ፓርቲ ተጠያቂ ነው ይላል።

የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ “ኢህአዴግ ያቋቋመው መንግስት መፍትሄ አይሰጥም ተባለ” በሚል ርዕስ ያወጣው ዜና ከዚህ እንደሚከተው ይነበባል:-

ኢትዮጵያ ውስጥ እየተስተዋለ ያለው ረሃብ የገዥው ፓርቲን ፖሊሲ ውድቀት ያሳያል ሲል ሰማያዊ ፓርቲ ከሰሰ፡፡

ኢህአዴግ ያቋቋመዉ አምባገነን መንግስት ለኢትዮጵያ መሰረታዊ ችግሮች መፍትሄ ሊሰጥ አይችልም ሲል ታቃዋሚዉ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ አስታወቀ።

የ2007ቱን የምርጫ ሂደት የተቹት አመራሮቹ ህግ ወጥ የሆነ ነገር እየተንከባለለ መጥቶ መንግሥት ምስረታ ላይ ደርሷል ብላል።

በተያያዘ ዜናም የፊታትን ቅዳሜና እሁድ በጠቅላይ ሚንስትር ደሳለኝ ኃይለማሪያም ሰብሳቢነት የሚካሄደው የእድገትና የለውጥ ሽግግር እቅድ ስብሰባ ላይ ቢጋበዙም የማይገኙ መሆናቸውን የተለያዩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች እየገለጹ ነው።

መድረክ የሰጠዉን መግለጫ የተከታተለው እስክንድር ፍሬዉ ተከታዮን ዘግቧል። ለማዳመጥ እዚህ ላይ ይጫኑ።

ይህ በ እንዲህ እንዳለ የሰማያዊ ፓርቲ “ረሃቡ የገዥው ፓርቲ የፖሊሲ ውድቀት ነው!” በሚል ርዕስ የሚከተለውን መግለጫ ሰጥቶዋል:-

ገዥው ፓርቲ ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ ህዝብ በቀን ሶሰት ጊዜ እንደሚመግብ ቃል ሲገባ ቆይቷል፡፡ በተለይ ባለፉት 10 አመታት ጀምሮ ኢኮኖሚውን በሁለት ዲጅት እያሳደገ እንደሚገኝ ልሳኑ ባደረጋቸው የመንግስት ብዙሃን መገናኛዎች በረሃብና በርዛት እየተሰቃየ ለሚገኘው ህዝብ መልሶ እየነገረ ይገኛል፡፡ ይሁንና ይህ ስርዓቱ ሀገሪቱን ወደመካከለኛ ገቢ ያደርሳል የሚለው እድገት ለጥቂት ጊዜያት በተከሰተና በተለመደ የዝናብ እጥረት የሚከሰትን ድርቅ እንኳ መቋቋም አቅቶት ዜጎቻችን በተደጋጋሚ የረሃብ ሰለባ ሲሆኑ ቆይተዋል፡፡

በተለይ በዚህ ወቅት በመላ ሀገሪቱ የተከሰተው አስደንጋጭ የረሃብ አደጋ ዜጎችን ለከፋ ስቃይና መከራ ዳርጓቸዋል፡፡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ከ7.5 ሚሊዮን በላይ ዜጎቻችን ለከፋ የረሃብ አደጋ ተጋልጠዋል፡፡ ከ40 ሺህ በላይ ህፃናት የረሃቡ ሰለባ ሆነዋል፡፡ ከግጦሽና ከውሃ እጥረት የተነሳ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የቤት እንሰሳት እየሞቱ ነው፡፡ ረሃቡ ባልጠናባቸው አካባቢዎች ሳይቀር አርሶ አደሩም ሆነ አርብቶ አደሩ ነፍሱን ለማዳን የእርሻ በሬዎቹን ሳይቀር ለገበያ እያቀረበ በርካሽ ዋጋ ለመሸጥ ተገዷል፡፡

ገዥው ፓርቲ ችግር ቢከሰት እንኳ በአደጋ ጊዜ ለዜጎች የሚበቃ እርዳታ አቀርባለሁ ሲል የነበረ ቢሆንም ለወገኖቻችን ግን የሚደርስላቸው አልተገኘም፡፡ ይባስ ብሎም ለዜጎች ዓለም አቀፍ ተቋማት እንዳይደርሱላቸው የተፈጠረው ረሃብ የራሱ የፖሊሲ ውድቀት መሆኑን የሚያውቀው ስርዓቱ የዜጎቻችን ስቃይና መከራ ሲሸፋፍን ከርሟል፡፡ ከአቅሙ በላይ ሲሆን ችግሩ እንደተከሰተ ቢገልፅም ለዜጎች ተገቢውን እርዳታ በሚያስገኝ መልኩ እርምጃ እየወሰደ አይደለም፡፡ በአሁኑ ወቅት በኦሮሚያ፣ በአፋር፣ በደቡብ፣ ትግራይ፣ በአማራ፣ በሶማሊና በሌሎቹም ክልሎች በተከሰተው ረሃብ ዜጎች ከፍተኛ ችግር ላይ ናቸው፡፡ ለተከሰተው የረሃብ አደጋ ተገቢው ትኩረት መነፈጉ ገዥው ፓርቲ እመራዋለሁ ለሚለው ህዝብ ደንታ ቢስነቱን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ረሃቡ፣ ርዛቱ፣ ድህነቱ፣ ስደቱ፣ ስራ አጥነቱ፣ የኑሮ ውድነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ዜጎችን በብርቱ እየተፈታተኑ በሚገኝበት ወቅት ገዥው ፓርቲና በስሩ ያሉ ድርጅቶች ተመሰረትንበት የሚሉትን ጊዜ ለወራት በቅንጦት በማክበት በብዙ ሚሊዮን ገንዘብ ከኢትዮጵያውያን ጉሮሮ ነጥቆ ድግስ ሲደግስና አሸሸ ገዳሜ ሲል በርካታ ኢትዮጵያውያንን አሳዝኗል፡፡

ለተከሰተው ረሃብ ኢህአዴግ ለይስሙላ ቆሜለታለሁ የሚለውን አርሶ አደርና አርብቶ አደርን ህይወት ለማሻሻል የረባ ስራ እንዳልሰራ ያረጋገጠ ነው፡፡ ግብርናው ኢኮኖሚውን ይመራል ቢልም እስካሁን ግን በየአመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የረሃብ ሰለባ እንደሆነ ቀጥለዋል፡፡ መሬት የመንግስት ነው በሚል ሽፋን አርሶ አደሩን ከቀየው እያፈናቀለ ለስርዓቱና ደጋፊዎችና ለባዕዳን መሬትን እየሸጠ አርሶ አደሩን ለረሃብ ተጋላጭ አድርጎታል፡፡ በስርዓቱ የፖሊሲ ውድቀት የተፈጠረውን አደጋ ለመሸፋፈን በሚያደርገው ጥረትም በርካታ ኢትዮጵያውያንን የችግሩ ሰለባ እየሆኑ ነው፡፡

ቢዘገይም ፓርቲያችን ሰማያዊ ገዥው ፓርቲ ለወገኖቻችን የሲቃ ድምፅ ጆሮ ዳባ ማለቱን አቁሞ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ እንጠይቃለን፡፡ በተለይ ስለ ችግሩ ለኢትዮጵያውያንና ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ስለ ረሃቡ በደንብ የሚያስረዳ ገለልተኛ አካል ተቋቁሞ ለዜጎቻችን መፍትሄ እንዲፈለግ እንጠይቃለን፡፡ ስርዓቱ ደካማና ኃላፊነት የጎደለው እንደመሆኑ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ኢትዮጵያውያንና የዓለም ማህረሰብ ከወገኖቻችን ጎን እንዲቆሙ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ በዋናነት ግን ይህ የኢትዮጵያውያን መከራ የመነጨው ከገዥው ፓርቲ የተሳሳተ ፖሊሲ፣ የአፈፃፀም ብቃት ችግርና ለኢትዮጵያውያንም ባለው ግድየለሽነት መሆኑን ተገንዝበን ይህን ለችግሮቻችን ምንጭ የሆነ ስርዓት በቁጥርጠኝነት መታገል እንዳለብን ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ድል የህዝብ ነው!

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

መስከረም 27 ቀን /2008 ዓ.ም

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. tsegaye jigso says

    October 10, 2015 11:58 am at 11:58 am

    good

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule