• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ብሶት የወለደው የኦሮሚያ አመጽ ተቆንጥሮ አስመራ ላይ ተላከከ!

February 29, 2016 06:39 am by Editor Leave a Comment

በኦሮሚያ የተነሳውን ህዝባዊ እምቢተኛነትና ዓመጽ ተከትሎ ስለጠፋው የሰው ህይወት እርግጠኛ አሃዝ የሚጠቅስ አልተገኘም። ዓለምአቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶችና የአገር ውስጥ ቀናቃኝ የፖለቲካ ድርጅቶች እንደሚሉት የህወሃት አንጋቾች ከ200 በላይ ንጹሃንን ገድለዋል። በነጻ አውጪ ስም አገሪቱን እየመራ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር – ህወሃት፣ አመጹን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠሩን በተደጋጋሚ ሲያስታውቅ ቆይቶ በስተመጨረሻ ችግሩን ቆንጥሮ አስመራ ልኮታል። ወታደርና ከባድ መሣሪያም ወደ ድንበር አስጠግቷል። መፍትሔው ጭፍን ብሔረተኝነት ሳይሆን ሁሉንም በሰብዓዊ ፍጡርነት ማየት ነው የሚሉ አካላት “ጆሮ ያለው ይስማ፣ ልቡና ያለው ያስተውል” እያሉ ነው፤ ርምጃቸውንም ከጊዜ ጋር አዋዝተዋል። ህወሃት የትጥቅ ትግልን የራሱ “ንግድ ምልክት” አድርጎ መውሰዱ የማይዋጥላቸው “ለህወሃት ብቻ የትጥቅ ትግልን ህጋዊ ያደረገው ማን ነው?” በማለት ይጠይቃሉ፡፡

“ታዛዥ” በሚል ስያሜ የሚጠሩትና ብዙም ከበሬታ የሌላቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ፣ “የማያዳግም ርምጃ እንወስዳለን” ባሉ ማግስት የተምታታ መግለጫ በመስጠት ዝነኛ እየሆኑ የመጡት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሃላፊ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ የምዕራብ አርሲውን ችግር አስመራ ላይ ለጥፈውታል። ሠራዊት አዝምቶ ንጹሃንን እየጨፈጨፈ ያለው ህወሃት፣ በሃይለማርያም ደሳለኝ አንደበት “የማያዳግም ርምጃ እንወስዳለን” ማለቱን ተከትሎ “እየገደሉ ነው፣ እያሰሩ ነው፣ እየገረፉ ነው፣ እያቆሰሉ ነው፣ የማያዳግም ሲባል ነፍሰጡር ከመግደል የዘለለ ምን አይነት ርምጃ ሊሆን ነው?” ሲሉ አስተያየት የሰጡት የአርሲ ኮፈሌ ነዋሪ ናቸው።

ሌላ ገለለተኛ አስተያየት ሰጪ “እኔ በግሌ ስርዓቱን የማላምንበት ደረጃ ላይ ደርሻለሁ፣ ብዙ ሰዎች ራሳቸው ኢህአዴጎቹን ጨምሮ ከነባለሥልጣኖቻቸው ልባቸው ሸፍቷል። አገር የሚመራ ድርጅት ካልታመነ አደጋው የከፋ ይሆናል” ሲሉ ስጋታቸውን ይገልጻሉ። ማሳያ በማቅረብ ሲቀጥሉም ሙሽሮች ቀስቃሽ ዘፈን አሰሙ በማለት ተኩስ በመክፈት ሠርገኞችን አቆሰሉ፤ ሙሽሮቹ ሸሽተው ጫካ ገብተው ከሁለት ቀን በኋላ ተገኙ፤ ህዝብ ተቆጣና ጠመንጃ አንግተው የሚገሉትን ገደለ፤ ይህን እውነት ለምናውቅ “ጉዳዩ ከሰላማዊ ተቃውሞ ያፈነገጠ ሽብር ነው ተብሎ ሲነገረን ምን እንበል? ከዚህ በላይ እምነትን የሚሸረሽር ምን አለ?” በማለት ይጠይቃሉ፡፡

ኢህአዴግ ከበረሃ ወደ ቤተመንግስት ሲዛወር የእድሜ ልክ ጠላቱ አድርጎ የሚያሰቃየውን አማርኛ ተናጋሪ ህዝብ ማስፈጀት የጀመረው አርሲ እንደሆነ የሚያስታውሱ ከፍሎች አሁን ህወሃት “ምዕራብ አርሲ ላይ የታየው የተለየ ሽብርና ስልጣንን ኢ-ህግመንግስታዊ በሆነ መልኩ ለመጨበጥ ያለመ ነው፣ በጉዳዩ ላይ የአስመራው መንግስት እጅ እንዳለበት ማስረጃ አለ” በሚል ለውጭ ሚዲያዎች መግልጹን በርካቶች አይቀበሉትም።

የቬንዝዊውላ አምባሳደር የሆኑት ራፋኤል ዳርዮ ራሚሪዝ ካሬኖ የማዕቀቡን ኮሜቴ ስራዎች አስመልክተው ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታ ምክር ቤት ሲያስረዱ፣ “ቡድኑ የኤርትራ መንግስት አልሸባብን እንደሚደግፍ የሚያሳይ ማስረጃ አላገኘም” ባሉ ማግስት ህወሃት ይህንን መሰል መረጃ ይፋ ማድረጉ መረጃውን የተዛባ እንደሚያደርገው እነዚሁ ወገኖች ይናገራሉ።

ከዚሁ ጋር በተያያዝ ይሁን በሌላ ህወሃት በሰሜን ጎንደር ሱዳን ድንበር ኤርትራ ላይ ያነጣጠረ ሰራዊትና ከባድ መሳሪያ ከወትሮ በተለየ መልኩ ማሰለፉ ተሰምቷል። ኢሣትና አንዳንድ ድረገጾች ዜናውን ይፋ ከማድረጋቸው ውጪ ከህወሃት በኩል በይፋ የተባለ ነገር የለም።

ኢሳያስ አፈወርቅን በማስወገድ ራሱ ያደራጀውን መንግስት ኤርትራ ላይ ለመትከል ደፋ ቀና ማለት ከጀመረ ዓመታትን ያስቆጠረው ህወሃት፣ ይሳካ አይሳካ ባይታወቅም በተመሳሳይ መልኩ ህወሃትን ለማሰወገድ የሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ ድርጅቶችን ሻዕቢያ ማገዙ እንደወንጀል ይቆጠርበታል። ተቃዋሚዎችን ማደራጀት የሽግግር መንግሥት መመሥረት ለህወሃት ህጋዊ ሲሆን፣ ለሻዕቢያ ወንጀል ተደርጎ ተወስዷል።

ህወሃት በተገንጣይ ስም የሚጠራበትን “ታላቅ የመሆን” ህልሙን እውን ለማድርግ ኤርትራ ላይ የራሱን ስሪት መንግስት ለማቋቋም ሌት ተቀን ሲሰራ፣ ሻዕቢያ ብዙም ሲከሰው አይሰማም። በኢትዮጵያ የውስጥ ችግር ሲባባስ ሻዕቢያን መወንጀል፣ ማስፈራራት፣ ማሳጣት፣ ተቃዋሚዎችን “ተላላኪ” በማለት ለማሳነስና ክብረቢስ አድርጎ ለመሳል መሞከር፣ ወዘተ የተለመደ የህወሃት ተግባር መሆኑ በተደጋጋሚ የሚሰማ ጉዳይ ነው።

ለዚህም ይመስላል የኦነግ ቃል አቀባይ አቶ ቶሌራ አዳባ ባለፈው ዓርብ ለቪኦኤ ሲናገሩ ይህንን ጉዳይ ያሰመሩበት። የሳዳም ሁሴን የማስታወቂያ ሚኒስትር የአሜሪካ ወራሪ ጦር ባግዳድን ሲቆጣጠር እሳቸው የመድፍ ድምጽ በሚሰማበት ስልካቸው “ችግር የለም” ዓይነት መልስ ይሰጡ ነበር። በሰሞኑ መግለጫቸው ከእኚሁ ሚኒስትር ጋር የተመሳሰሉት አፈቀላጤ ጌታቸው ረዳ ለሰነዘሩት ክስ መልስ የሰጡት አቶ ቶሌራ “ስልጣን ላይ በመቆየታቸው የነበሩበትን ሁኔታ የዘነጉ ይመስላሉ። ለህወሃት የትጥቅ ትግልን ህጋዊ አድርጎ ኦነግን የሚከለክል ህግ የለም” ብለዋል።

ተመሳሳይ ጥያቄ የሚያነሱ ወገኖች በምዕራባውያን ዕርዳታ፣ ድጎማና በኢትዮጵያ ላይ ባላቸው ጥላቻ እየተደገፈ “የትጥቅ ትግል አካሂጄ ድል አደረኩ” የሚለው ህወሃት የትጥቅ ትግልን የራሱ ብቸኛ “የንግድ ምልክት” አድርጎ መውሰዱ የማይሠራና አሁን ኢትዮጵያ ካለችበት ሁኔታ አኳያ ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ ይከራከራሉ፡፡ እነዚሁ ወገኖች እንዲያውም ይህ የህወሃት አስተሳሰብ ነጻነትን የመጎናጸፊያው ብቸኛ መንገድ የትጥቅ ትግል ነው ብለው እንዲያምኑ በርካታዎችን እያደረጋቸው እንደሆነ ያስረዳሉ፡፡

ከፋሽስት ጣሊያን ባልተናነሰ ሁኔታ ህጻናትን፣ ነፍሰጡርን፣ አዋቂዎችን፣ አረጋውያንን፣ የሚጨፈጭፍው ወያኔ ወንጀሉን ለመሸፋፈን የሚያደረገው መፍጨርጨር መሆኑንን በመግለጽ የቀረበባቸውን ክስ ያጣጣሉት የአርበኞች ግንቦት 7 የውጭ ግንኙነት ሃላፊ ነዓምን ዘለቀ “ጌታቸው ረዳና መሰሎቹ ለፍርድ የሚቀርቡበት ቀን ሩቅ አይሆንም” ሲሉ ህወሃትን ራሱ “መንግሥታዊ አሸባሪ ነው” ሲሉ ጠርተውታል።

ኦፌዴንም ከፊል አባሎቹ አሸባሪ ተብለው መከሰሳቸውን አስመልከቶ ድርጅቱ ከሽብር ጉዳዮች ጋር ግንኙነት እንደሌለው፣ አምባገነንነትን እንደሚዋጋ፣ ሕዝብ ለሚያቀርበው ጥያቄ አግባብነት ያለው መልስ መሰጠት እንዳለበትና ብቸኛውም አማራጭ ሕዝብን ማክበር መሆኑንን በመግለጽ የጌታቸው ረዳን ስሞታ አጣጥለውታል።

በአገር ውስጥ የተከሰተውን ሕዝባዊ ተቃውሞ ወደ አስመራ መውሰድ እና ከኤርትራ ጋር ማዛመድ በኦሮሚያ ላይ “የማያዳግም ርምጃ እንወስዳለን” የሚለውን የህወሃት አካሄድ “ሕጋዊ” ሽፋን ለመስጠት የታሰበ እንደሆነ ይነገራል፡፡ በአገር ውስጥ ያሉ የፖለቲካ ታዛቢ ለጎልጉል በሰጡት አስተያየት መሠረት “ኤርትራ አሸባሪ ከተባለች በኋላ የኦሮሚያ ተቃውሞን ከኤርትራ ጋር ማዛመድ በቀጣይ ለመውሰድ ለታሰበው እርምጃ “አሸባሪነትን ለመከላከል የተወሰደ” የሚል የአገር ውስጥና ዓለምአቀፋዊ ሕጋዊ ሽፋን ለመስጠት ያስችላል፤ አሜሪካ አፍጋኒስታንን አሸባሪ ካለች በኋላ ድንበር አልፋ፤ ባሕር አቋርጣ አፍጋኒስታንን ለመደብደብ ሕጋዊ ሽፋን እንዳገኘች ሁሉ ይኼኛውም የህወሃት አካሄድ ከዚህ ጋር ተመሳሳይነት አለው” ብለዋል፡፡ (ፎቶ: ተስፋዜና)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule