• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የኔ” የምለውን፤

May 12, 2014 06:18 am by Editor 4 Comments

ባለፈው “ምን ይባላል?” በሚል ርዕስ ላቀረብነው የብሌን ከበደ ግጥም በመሳተፍ ጨዋታውን በግጥም ላደመቃችሁት Yaredo Enkubi እና በለው ምስጋናችን የላቀ ነው:: ሌሎችም በፌስቡክ ገጻችን በኩል አስተያየት የሰጣችሁንን ከልብ እናመሰግናለን:: ለዛሬ ደግሞ የዘወትር ተሳታፊያችን የካናዳው ከበደ ይህንን ግጥም ለከውንናል – “የኔ” የምለው በማለት ለላኩልን ግጥም እናንተስ ምን ትላላችሁ? “የኔ” የምትሉትን በማለት ጨዋታውን እናድምቀው – ሃሳባችንን እንንወጣው – የልባችንን እንግለጽ::

“የኔ” የምለውን፤

ታሪኬን ኩራቴን
መብቴን ነፃነቴን
…ኢትዮጵያዊነቴን

ከውስጤ አውጥታችሁ
መሬቴን ወስዳችሁ፤ ቤቴን አፍርሳችሁ

መንገድ ብትሠሩ
ፎቅ ብትደረድሩ

ቢትረፈረፍ እንኳን

መብራቱ ባቡሩ

እኔ “የኔ” ብየ እስካልተቀበልኩት፤

እስካልያዝኩት ድረስ

ምንም አይመስለኝም

ቢነድ፤ ቢቃጠል፤ ቢናድና ቢፈርስ

ትዕግሥቱ ሲሟጠጥ

ሰው ሲቆርጥ ተስፋ

ተመልከት ሲሪያን፤

አገር በልጆቿ እንደምትጠፋ

(የካናዳው ከበደ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    May 12, 2014 12:38 pm at 12:38 pm

    ***************
    ታሪከ! ነፃነት! ክብር! ዜግነትማ! ተገፎ ተዋርዶ
    ሕዝብ እየተናቀ ገንዘብና ጉልበት ህብሪትን ወልዶ
    ለመኖር ለመሄድ መናገር ለቀብር ለምኖ አስፈቅዶ
    ተገዛም ተሰጠ ፍቅረ-ንዋይማ ስብዕናን ወስዶ
    በቋንቋ በዘር በአሳላጭ ተጫጭቶ በጥቅም ተሞዳምዶ
    በሙስና ፍቅር በመሬት ተጣልቶ በሕንፃው ላይ ተዋዶ
    ከሰው የበለጠው የድንጋይ ክምር ዋሻ ነው ወይ ነዶ !
    ___—-___——___አዎን!
    ሲዘርፉ ሲግድሉ ሲበሉ ለእናንተ ነው ሲሉን
    የእናንተ የእኛ በእኛ ለእኛ ብቻ ይሆናል ያሉን
    በጥቅም ሲጣሉ ሲሻሙ ሲቃሙ እሪ በሉ የሚሉን
    የጠገበ እርስ በርሱ ይባላል የተራበ ይበላል መሪውን
    የማን ነው ብለን ነው ዘራፍ በሉ ያሉን!?
    ከቶ ለማን ብለን? አባሉን እንጂ መች አበሉን?አስበሉን?
    አውቀነዋል ለምን ባልበላ አንጀታችን ሙት እያሉ የሚምሉልን ።
    በለው! ከሀገረ ካናዳ

    Reply
  2. Mohammed Seid Ali says

    May 13, 2014 10:24 pm at 10:24 pm

    ደግ ተንፍሰሃል የካናዳው ከቤ፤
    ይህ የኔም ሃሳብ ነው የነፍሴ የልቤ፣
    ግንኮ ወዳጄ እኔ የኔ ምለው አለኝ ብዙ ሀብት፤
    አንበሽብሾኝ የለ ፀሃዩ መንግስት፤
    ቢፈርስንኳ ቤቴ መልሶ እንዲለማ፤
    ሰጥቶኛል ቅሊንጦን አሲዮ ቤሌማ፤
    አባይም ይገደብ ዛሬ እኔ ታርዤ፤
    ነገ እቀዳዋለሁ ጀሪካኔን ይዤ፤
    ስደትም የኔ ነው ስቃይ እንግልት፤
    አስፓልቱም ይደልደል ነገ ባደባባይ እንድሞትበት፤
    ኢቲቪም የኔ ነው ፋናየም የኔው ናት፤
    የተኸለቁልኝ ስሜን ለማጠልሸት፤
    አጋዚው ልዩ ሃይል ፌዴራል ፖሊሱ፤
    በየኮሌጆቼ ፈጥነው የሚደርሱ፤
    አሉኝኮ አስጠኚ ሂሳብ ኬሚስትሪ፤
    እያገላበጡ በጥቁር ጉማሬ፤
    ከፈለኩኝ ደግሞ ለነፍሴ ማደር፤
    በየመስጊዶቹ ገዳማት ደብር፤
    ቁርአን የሚያቀራ ወንጌልን የሚሰብክ፤
    ልማታዊ ካድሬ ፂሙን አንዠርግጎ ቆቡን አርጎ ልክክ፤
    አለኝ ቄስ ቃልቻ የሽፈራው ምሩቅ፤
    የሚያቃርብ ሳይሆን ከጌታ የሚያርቅ፤
    እና ወዳጄ ሆይ እኔ የኔምለው፤
    የወያኔ መንግስት ዘርቶ ያበቀለው፤
    አለኝ አለኝ አለኝ እልፍ ወአእላፍ፤
    አንዷን ካጎደልኩኝ ቶርች የሚያስገርፍ።

    Reply
  3. Bombu says

    May 19, 2014 10:24 pm at 10:24 pm

    የካናዳው ከቤ ያቀረብከው ግጥም
    ካርስቱ ጀምሮ በቁምነገር ፍርጥም
    ያለ ስለሆነ እኔም ወድጃልሁ
    ይልመድብህ ብዬ ወደኔ መጣልሁ

    እንደኔ ከሆነ እንደተራ ዜጋ
    ሰማይ መሬት ወርዶ ባግድም ቢዘረጋ
    ኣይደለም ሥርዓት የሕዝብ ድጋፍ ያጣ
    እምቢ ለዜግነት እረ ማንም ይምጣ

    የሥልጣኔማ መነሻው ከድሮ
    ሓገር መንግሥት ዜጋ ባንድነት ተሳስሮ
    ነበረ ዕውቀቱ ከውነት መዳረሻ
    ይባስ በኢትዮጵያ በስው ዘር መነሻ»

    Reply
  4. አሥራደው (ከፈረንሳይ) says

    May 24, 2014 12:19 am at 12:19 am

    “የኛ” ነው! “የኛ” ነው! – “የኛ”ነው የ’ኔ ቃል፤
    “የኔ” እምለው የለም – “የ’ኛ” ይበልጥብኛል::
    ያንቺ የሷ ይሁን – የነሱ ለነዚያ፤
    አብሮነት አንድነት – ይሁነን መመሪያ፤
    ያንተ የኔ ሆኖ – የኔ ያንተ ይሁን፤
    ኢትዮጵያ የኛ ናት – እኛም ያገራችን::
    ወዳጅ እንዲያከብረን – ጠላት እንዲፈራን፤
    በጋራ አብሮ መኖር – “እኛ” ነው እሚበጀን::
    የ’ኔ የ’ኔ ቀርቶ – የ’ኛ ስንባባል፤
    ፍቅራችን ያብባል – አገርም ይለማል::

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule