• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሌባዬ. . .

September 28, 2012 06:15 am by Editor 4 Comments

ሌባዬ. . .
ድምጹ ሳይሰማ ኮቴውን አጠፍቶ
በጠራራ ፀሐይ የደጄን በር ከፍቶ
መዝለቅ የጀመረው ክርችም በሬን ከፍቶ
ምን ሊዘርፈኝ ይሆን በምኔ ጎምጅቶ?

በማለት ኖላዊት ሽመልስ ስትጠይቅ የሚከተሉት መልሶች ተሰጥተዋታል፡፡
(ምልልሱን ያገኘነው ከፌስቡከ ሲሆን እርስዎም የሃሳብ በመስጫውን በመጠቀም ምላሽዎን እንዲሰጡ እንጋብዝዎታለን፡፡)
*************************************************************************************
ጠንቀቅ
አለሽ ንብረት አለሽ
አንቺዬ ሃብት አለሽ
ገንዘብ የማይገዛው
ለራስሽ ያልታየሽ
እጅግ የበለጠ
ከወርቅ፤ አልማዝ፤ ከእንቁ
አድፍጦ ሊዘርፍሽ
ያመጣው ከሩቁ
እመኚኝ ሃብት አለሽ
ዘብ የሚያስፈልገው
ብቻ ችላ ብለሽ እንዳታሰርቂው፡፡
(ብሌን ከበደ)
***************************************************************************************
በጠራራው ፀሀይ ሊዘርፍሽ የመጣ
ምን ዓይነት ደፋር ነው ምን ዓይነት ፈጣጣ!
በይ ጠንቀቅ ብለሽ ልብሶችሽን ሳይሆን ልብሽን ጠብቂ
ወርቁም ጌጡም ያለው እዚያው ነው እወቂ
እኔ ነግሬአለሁ ኋላ ተጠንቀቂ!
(ሁዳድ ንጉሤ)
**************************************************************************************
የተረፈችውን ስንቴ ተቆንጥራ
እንዳታልቅ ስሰስት ስተባ ስፈራ
ልቡን አደንድኖ ለልቤ ሳይራራ
ሊዘርፍ ይሄ ደፋር መጣ በጠራራ
(ቡቲካ ሽመልስ)
**************************************************************************************
ምን አይነት ደፋር ነው
shame እንኳን የሌለው
ሌባን ሌባ መስረቁ
ነበረ የሱስ ድፍረት
ይሄን ጠንቅቆ አለማወቁ
ቅኔ ምትደረድሪ
እንደሆንሽ ዘራፊ
ይህን አላውቀ የሌባ ጀማሪ
ሊዘርፍሽ የመጣው
እልም ያልሽ ዘራፊ
መሆንሽን አረ ማን ይንገረው?
(ኤልሳ ተገኔ)
**************************************************************************************
ቶማስ ለማ ለቡቲካ ሲመልስ፡-

ባጉል ቀን ተለክፎ
አካላቱ ዝሎ ፣ ሰዉነቱ ሰንፎ
የጣለዉን ዕቃ
ሊፈልግ ቢመጣ
አወይ “ያንች ነገር” ሌባ አስባለው በቃ
************************
አበባሽን ይዘሽ ፣ በቀን ስትዞሪ
ቢመጣ በቀፎሽ ፣ ንብ ሆኖ ማር ሰሪ
እንጀራ ጋጋሪ
ሌባ ማለት ትተሽ ፣ ጓዳዉን መርምሪ
በጎድኑ ግቢ ፣ በክፍተቱ ቅሪ
በቀን የሚገኝ ነው ፣ ፍቅር እዉነትን አብሪ
(ዘገብረየሱስ መስከረም 2004)

(ምልልሱን ያገኘነው ከፌስቡከ ሲሆን እርስዎም የሃሳብ በመስጫውን በመጠቀም ምላሽዎን እንዲሰጡ እንጋብዝዎታለን፤ ታዲያ በግጥም መሆኑን አይዘንጉ፡፡)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Tsinat says

    September 28, 2012 08:25 pm at 8:25 pm

    እሺ እንዲህ እንበል እሱማ ተሳስቶል
    ንብረት ያለሽ መስሎት ሊዘርፍሽ ከጅሎል
    እጅግ የሚገርመዉ ያንቺ መደንገጥ ነዉ
    ንብረት እንደሌለሽ ልብሽ እያወቀዉ

    Reply
  2. Gedion Adenew says

    September 28, 2012 09:57 pm at 9:57 pm

    Anchim minim yelesh-Lesum kentu lifat
    Berishin kerchimesh-Lik ende balehabt
    Layagegn layzerfish- Kenu alefebet!!!

    አንቺም ምንም የለሽ – ለሱም ከንቱ ልፋት
    በርሽን ከርችመሽ – ልክ እንደባለሃብት
    ላያገኝ ላይዘርፍሽ – ቀኑ አለፈበት፡፡

    Reply
  3. Tsinat says

    September 29, 2012 02:17 am at 2:17 am

    የቆለፍኩትን በር ይበርግደዉ ይግባ
    ለማግኘት ከቻለ አንዳች የሚረባ
    እስኪ ቆዩኝማ ምን ይሁን ብይ ነው በሬን የከረቸምኩ
    አልማዝ እንደሸሸግኩ ወርቁን እንደደበቅኩ?
    የቤቱ ባዶነት ልቤ እያወቀዉ ለካስ በከንቱ ነዉ በቴን የከረቸምኩ

    Reply
  4. Abe, says

    October 5, 2012 07:55 pm at 7:55 pm

    ሥረቃት! ስረቃት!
    በጎን የምትወጂው
    እስከሆነ ድረስ
    ቢጎተት ?!
    ቢመለስ ?!
    ያሻውን ቢቆምጥ?!
    ከሌባሽ ሌብነት
    ተማርከሽለታል
    ተሰርቀሽለታል
    በጠፍ በጨረቃ
    “ይዘኸኝ ሂድ” አይነት
    አቆላምጠሸ ጠርተሸ
    ሌባሽ ከሆነልሽ
    አንቺን የሚከፋሽ
    ባይሰርቅሽ እንደሆን ልቤ ጠርጥሮታል
    ሂድ!? በሚለው ቃልሽ ናልኝ ብሰሺዋል
    ሌባዋ ሂድላት
    ስረቃት! ስረቃት!
    (አበበ አዲስ)

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule