• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሽብርተኛ ከሳሹ ሽብርተኛው የወያኔ መንግስት

March 8, 2013 02:11 am by Editor Leave a Comment

የመጨረሻ ግባቸው የእስልምናን መንግስት ማቆም ነው ብሎ የወያኔ አስተዳደር ያቀረበውን የተቀነባበረ ፊልም ( ጃሃዳዊ ሐረካ) በመደነቅ አየሁት። ወያኔ ማለቴ እስካሁን እራሱን ነጣ አውጪ እያለ የሚጠራው የትግራይ ቡድን ኢሃድግ የሚል ማወናበጃ ስም በመረከቡ ነው፡

የተሰጠው መረጃ ውሸት ለመሆኑ ተጨባጭ ማስረጃ ማቅረብ ባልችልም የመረጃ አቅራቢው ውሸታምነት በመረጃ በማስደገፍ ለማቅረብ እሞክራለሁ።

መረጃቸውን በቴሌቭዥን የሚያቀርቡት አማን አሰፋ፣ አቡበከር አህመድ፣ ከሚል ሸምሱ፣ያሲን ኑሩ፣ ሙፍቲ አህመድ … የሚዘረዝሩት ታሪክ ወያኔ ራሱ ጥፎ ያቀረበላቸው ሊሆን እንደሚችል መገመት አያዳግትም። ከዚህ በፊት እነ ብርትኳን ሚደቅሳ፣ ፐርፌሰር መስፍን፤ ዶ/ር ያዕቆብ… ታላላቅ ልናከብራቸው የሚገቡ ጋዜጠኞች እንደነ እስክንድር ነጋ የመሳሰሉ ሁሉ በሽብርተኛነት በመታሰራቸው፤ ወያኔ የሚቃወመውን ሁሉ ያለህግ ለማጥፋት ሲያስብ ይህንን ውንጀላ መጠቀም ከጀመረ ውሎ በማደሩ ይህኛውም ውንጀላ ከዚህ ያልተለየ እንደሚሆን ጥርጥር የለኝም፡ ከሳሽ ፈራጅና ቀጪም ወያኔ ራሱ ነው አቀነባባሪውም የብሄራዊ መረጃ አገልግሎት ነው። በአገሪቱ ውስጥም የሕግ የበላይነት ባለመኖሩ ሁኔታውን መርምሮ ለሕዝብ ማቅረብም አይቻልም። የጸረ ሽብርተኛ ሕግ በማለት ወያኔ ከወነጀላቸው ጋር (ያለምንምንም መረጃ) ግኑኝነት ማድረግ ከ 10 እስከ 15 ዓመት ያስቀጣል ይላል።

ያወጣውን ሕገ መንግስት በመናድ ተወዳዳሪ የሌለው ወያኔ፤ በራሱ ሕገመንግስትና ባለራዕዩ መሪ ደጋግመው ፊልሙም ላይ እንዳስረዱት መንግስት በሃይማኖት ጣልቃ አይገባም እየተባለ ቢደሰኩርም በክርስቲያኑም ሆነ በእስልምናው ሃይማኖት ገብተው ሲፈተፍቱ እናያለን።

በክርስትናው ሃይማኖት ጳጳሱን ከአገር አባረው የራሳቸው ቢሾሙም ተሿሚው ከዚህ ዓለም በሞት ቢለዩም ሌላ ጳጳስ ለወያኔ የሚያጎበድድ እስኪገኝ ሽር ጉድ እየተባለ ነው፡ “ አባይ ጸሐዬም የቀድሞውን ጳጳስ ማምጣት መንግስቱን እንደማምጣት ነው” ይህ አባባል ከመንግስት ተወካይ የተሰጠ ነው!! ሌላው የወያኔ ቁንጮ ሽማግሌው ስብሃት ነጋ “ የአማራና የክርስትያን አገዛዝ ቀብረነዋል ብሏል” እነዚህን መረጃዎች ይዘን መንግስት በሃይማኖት ጣልቃ አይገባም ማለት የዋህነት ነው።

የአዲሱን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የጳጳስ ምርጫ ካጤነው ስለመንግስት ያለንን ግንዛቤ ያጠናክርልናል።

መንግስት ሰለሚሰራቸው የፊልም መረጃዎች ለመጥቀስ

በሐውዜን (ረቡዕ june 1988) እንጀምር ፤ ይህ ጭፍጨፋ ሲካሄድ ወያኔ ለፖለቲካ ትርፍ ሲል ወገኔ የሚላቸውን የትግራይን ሕዝቦች፤ ከከተማ እንዳይወጡ መውጫውን ዘግቶ፤ ለደርግ ቀኑን አስታውቆ ለፊልም ቀረጻ ያዘጋጃቸውን ፊልም ቀራጮች ቁልፍ ቦታ ካስያዘ በሗላ የደረሰውን የቦምብ ድብደባ በዕለቱ ከሱዳን እንዲተላለፍ አድርጓል።

ሁለተኛው ድራማ አኬልዳማ የተሰኘው ነው (2011)፡ ( አኬልዳማ በደም የተበከለ ምድር ማለት ነው) የቃሉን መሰረት ወንጌል ላይ የሐዋርያት ስራና ማቴዎስ ወንጌል ላይ ይመልከቱ፡ ወያኔ ግን ይህንን ፊልም የሰራው አንዳንድ የፖለቲካ ተቀናቃኞቹን እስር ለመክተትና ህገወጥ ድርጊቱን ሕጋዊ ልብስ ለማልበስ ነው።-….የኦነግ የሽብር ቅጣት በበደኖ 1984፣ በሐረር የወያኔ አካል በነበረው የኦሮሞ ተገንጣይ ቡድን አማራው ላይ ጭፍጨፋ ሲያካሄድ፣ እርጉዝ ሴቶች ከነሕይወታቸው ሆዳቸው እየተቀደደ ሽሉ ሲወጣና ከዚያም በሗላ በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ መመሪያ ሲሰጥና ፊልም ሲያነሳ ከርሞ፤ ያንኑ ፊልም ከዓመታት በሓላ አሸባሪዎች እንዲህ አደረጉ ብሎ አሳይቶናል። ከዚህ ትያትር በሗላ እነ አርቲስት ደበበ እሸቱ፣ አቶ ስለሺ ሃጎስ….በሽብርተኝነት ተፈርጀዋል። አቶ ዲማ ነገኦም የግዜው የኦነግ መሪ ስለበደኖ ጉዳይ ገለልተኛ ምርመራ እንዳይካሄድ ወያኔ መከልከሉን አሳውቀዋል። ( ሽግግር ምክር ቤት ጉዳዩ ተነስቶ ኦነግ እንዲጣራ ቢጠይቅም ጉዳዩ እንዳይጣራ ወያኔ ከለከለ ይላሉ) አርሲ እስላሞች ክርስታያኖችን ጨፈጨፉ ብሎ በቀረበው ዜና የእስላም ሽርጥ ያሸረጡ የወያኔ ወታደሮች ክርስትኖችን እያሳደዱ ሲገድሉ ታይተዋል ከሞቱትም ላይ የወያኔ የፖሊስ መታወቂያ ከኪሳቸው ተገኝቷል፡

ወያኔ ከ424 በላይ የተማሩ አኙዋኮችን መሬታችን እየተዘረፈ ለውጭ ሰዎች መቸብቸብ የለበትም ስለ አሉ ለአረብና ለሕንድ መሬቱን ለመቸብቸብ አይመቹኝም ሌላውንም ያስነሱብናል በሚል ያደረገባቸውን ጭፍጨፋ መረጃው በጄኖሳይድ ዎች እጅ ይገኛል፤ ይህን ያህል ሽብር የፈጠረ ሽብርተኛ ከወያኔ በስተቀር ኢትዮጵያ ውስጥ ሌላ ቡድን የለም።

በማንኛውም መመዘኛ በመንግስት ደረጃ ስልጣን ይዞ ሰላማዊ ሕዝብን እንደ እንስሳ ካልተገዛችሁልኝ የሚል ሽብርተኛ መንግሰት፤ የራሱን ወገን አንዱን ጎሳ ከሌላው ጎሳ በፖሊሲ የሚያጋጭ፣ ያ ሳይሳካ ሲቀር አሁን ደግሞ በሃይማኖት ሊያተራምስ የተቀመጠ መንግሰት ነው፤ ለስልጣኑ እስከተመቸው ድረስ ማንኛውንም ወንጀል ከመስራት ወደሗላ የሚል መንግስትም አይደለም።

መልዕክቴ መንግስት በሚያሰራጨው ከአሉባልታ ያልተሻለ መርዘኛ ዜና እርስ በርስ ልንጠራጠር አይገባም። መታገል ያለብን ይህንን ሽብርተኛ መንግስት ለማስወገድ ስለሆነ፤ በዘር፣በጎሳ በሃይማኖት…ልንከፋፈል አይገባም፤ ኢትዮጵያችን ሁላችንንም ልታስተናግድ የምትችልና ስታስተናግድም የኖረጭ አገር ናት።

ታዛቢው

ከሆላንድ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule