• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ድሆች በደሃ ወገኖቻቸው ላይ ዘመቱ!!

December 15, 2015 02:16 pm by Editor Leave a Comment

“…. የመከላከያ ሰራዊት አባላት የተገነባው በደሃ ልጆች ነው። እባካችሁን እንደናንተው የድሃ ልጆች ወገኖቻቹህን አትግደሉ። ተንደላቃችሁ የምትኖሩም ለዚህ ህዝብ ራሩለት። ለራሳችሁ ጥቅም ስትሉ ይህን ህዝብ አታስፈጁት…” ሲሉ አቶ በቀለ ገርባ ለኢህአዴግ የመከላከያ ሰራዊትና ለህወሃት ታማኝ አገልጋይ ሹመኞች ጥሪ አስተላለፉ። አሁን በተያዘው መንገድ ከተቀጠለ ለማንም አይበጅም ሲሉ በግልም ሆነ በጋራ ህዝብን የሚያከብር ታሪካዊ ውሳኔ እንዲወስኑ ተማጸኑ። አቶ ኦባንግ ሜቶና አርቲስት ታማኝ በየነ “የሞቱት ዜጎች ሞት የሁላችንም ሞት ነው” ሲሉ ሁሉም ያገባኛል በሚል ስሜት ድጋፍ እንዲሰጥ ጥሪ አቀረቡ።

አቶ በቀለ በዲሰምበር ፩፫ ቀን ፳፩፮ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት፣ መከላከያ ሰራዊት ማለት ህዝቡን ከአምባገነኖች የሚታደግ እንጂ የራሱን ህዝብ የሚገድል ባዕድ ሃይል አይደለም ብለዋል፡፡ “ለምን እንደ ባዕድ መታየት ትፈልጋላችሁ” በማለት የጠየቁት አቶ በቀለ “እባካችሁ ራሩ” ሲሉ ለምነዋል።

“የድሃ ልጅ በድሃ ላይ እንዲዘምት መደረጉ ያሳዝናል” ሲሉ ሃዘን በተሞላበት ስሜት የተናገሩት የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር “በአሰቃቂ ሁኔታ ልጆቻቸውን እየመገቡ ጦማቸውን የሚውሉ ወላጆች በሚኖሩበት አገር እናንተ ተንደላቃችሁ የምትኖሩ ራሩ” በማለት ሁሉም ጊዜና ወቅቱን በመመርመር ወደ ልባቸው እንዲመለሱ አሳስበዋል። አያይዘውም “እባካችሁ እግዚአብሔርን ፍሩ” ሲሉ ከራሳችን አገርና ከሌሎች አገራት ትምህርት እንዲወስዱ ተማልደዋል።

armyለህዝብ ርህራሄ የሌላቸው አንድ ቀን በሃላፊነት እንደሚጠየቁ ያሳሰቡት አቶ በቀለ አጠንክረው ተናግረዋል። ከ፶ በላይ ዜጎች መገደላቸውን፣ መረጃው ሲሰበሰብ የሟቾች ቁጥር እንደሚጨምር በመግለጽ የችግሩን ስፋት አሳይተዋል።

በተመሳሳይ ርዕስ ኢሳት ያወያያቸው አቶ ኦባንግ ሜቶና አርቲስት ታማኝ በየነ የአንድ ኢትዮጰያዊ ሞት የሁላችንም ሞት ሆኖ ሊሰማን እስካልቻለ ድረስ ኢትዮጵያዊነት መገለጫው ምን ሊሆን ነው ሲሉ ጠይቀዋል። የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ “ህወሃት ገና ከጅምሩ መግደል ሲጀምር ሌሎች በኅብረት ቢቃወሙ ኖሮ ዛሬ ደረጃ ላይ አይደረስም ነበር” ሲሉ የህብረትን አስፈላጊነት አስምረውበታል።

አርቲስት ታማኝ በየነ በበኩሉ ዋቢ መረጃዎችን በማጣቀስ የህወሃትን ገበና ካስታወሰ በኋላ “አንዱ ሲሞት ሌላው ዝም የሚል ከሆነ ሞት በእያንዳንዳችን ደጅ ትመጣለች፤ ባርነቱም ይቀጥላል” ሲል በሰውነት ደረጃ ብቻ እንኳን ሃዘኔታችንን ልንገልጽ እንደሚገባ አመልክቷል። “መቃወም እንዴት ያስገድላል” ሲል ጠይቆ “ጥቂቶች ይሉናል፣ እነሱ ናቸው ወይስ የሚቃወሟቸው ናቸው ጥቂቶች” በማለት ይመልሳል። እንደገናም “የሚመሩን ፲፻ አይሞሉም” ይልና በመገረም በ፻ ሺህ የሚቆጠርን ህዝብ “ጥቂቶች” ሲሉ መስማት በህዝብ ላይ የመዛበት አይነት እንደሆነ ያሳያል። ህብረት አስፈላጊ ነው ሲል ጥሪውን አቅርቧል።

“ነጻ መውጣት መብት ነው” የሚል የቆየ እምነት ያላቸው የሰላማዊ ትግል አራማጁ አቶ ኦባንግ “ከሳጥናችን ካልወጣን ዋጋ የለንም” ሲሉ አሁን ሁሉም ያለው “ምን አገባኝ” በሚል ሳጥን ውስጥ እንደሆነ አስረድተዋል። አንዱ ላይ ጉዳት ሲደርስ፣ አንዱ ሲገደል፣ አንዱ ሲነካ ዝም ማለት የህወሃትን እድሜ እንዳረዘመው የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ኦባንግ አመልክተዋል።

“ቅኝ ወራሪዎች መጀመሪያ የሚወሩትን አገር ይከፋፍላሉ” ያሉት አቶ ኦባንግ “አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው አገዛዝ፣ የቅኝ ገዢዎቹ ቀለም ተመሳሳይ ከመሆኑ በቀር ከደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ አገዛዝ ተለይቶ አይታይም” ሲሉ አገሪቱን እየገዛ ያለውን የትግራይ ህዝብ ተገንጣይ ቡድን ተመሳሳይ ስልት እየተጠቀመ መሆኑን ተናግረዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule