• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዕርቅና ድርድር ቢያይዋቸው፤ ቢያይዋቸው!

January 21, 2017 05:20 am by Editor 3 Comments

(ርዕሰ አንቀጽ)

ላለፉት ሃያ አምስት ዓመታትና ከዚያም በፊት ስለዕርቅ ያልተናገረ የፖለቲካ ቡድን የለም ለማለት አይቻልም፡፡ ደርግ ስለ ዕርቅ ተጠይቆ አልሰማም አለ፡፡ ህወሃት/ኢህአዴግም የአገዛዝ መንበሩ ላይ ከመቆናጠጡ ጀምሮ ስለ ዕርቅ ይወራል፡፡ አዳዲስ የሚፈለፈሉ የተቀናቃኝ ድርጅቶች በአገር ውስጥም ይሁን በውጪ ስለ ዕርቅ ያወራሉ፡፡ የገባውም ያልገባውም ስለ ዕርቅ ይናገራል፤ ይሰብካል፤ ያስተምራል፤ … ይህንን ሁሉ አልፎ “እኔም ያገባኛል” በማለት ህወሃትም ስለዕርቅ ያወራል፡፡ ከማውራትም አልፎ ያስተምራል፤ ያሠለጥናል፡፡ ሰላማዊ ጦርነት፤ ጥቁር ብርሃን፤ እንደሌለ ሁሉ ህወሃትና ዕርቅም እንደዚያው ናቸው፡፡

ስለ ድርድርም እንዲሁ ይወራል! አሸማጋይ፤ አደራዳሪ፤ አወያይ በሌለበት እንወያይ ይባላል፡፡ ሁሉንም የተቆጣጠረው ህወሃት የሚደራደሩ ተቃዋሚ ሳይሆኑ “ተጠቃሚ” ፓርቲዎችን ከመፍጠር ጀምሮ፤ አደራዳሪ፤ ተደራዳሪና ሸምጋይ ሆኖ ይቀርባል፡፡ ሥርዓት ያወጣል፤ በዚህ ተመሩ ይላል፤ አልመራም ያለውን ወደ እስር ቤት ይመራል፤ ድርድሩ አሁንም በህወሃት የበላይነት ያበቃል፡፡

የተቀናቃኝ ፖለቲካ አመራሮችን በየእስር ቤቱ እያሰቃዩ ድርጅቶችን ለድርድር መጥራት ምን ማለት ይሆን? መቼም ህወሃት/ኢህአዴግ እስር ቤት እየሄደ ሊደራደር እንዳላሰበ ግልጽ ነው፡፡ የፓርቲዎቹስ አመራሮች ይህችን ያህል ቀዳዳ ስላገኙ መስክ እንደተለቀቀ ጥጃ የሚያስቦርቃቸው ምንድነው? የህወሃት/ኢህአዴግ ቅድመ ሁኔታ ማንሳት? ሲጀመር ለምን ቅድመ ሁኔታ ተቀመጠ? ሲቀጥል መቼ ተነሳ? እውነት ይነገር ከተባለ ማነው ቅድመ ሁኔታ ማስቀመት ያለበት? ህወሃት/ኢህአዴግ ወይስ ተቃዋሚዎች? አመራሮቻቸው እና አባሎቻቸው በየእስርቤቱ እየተሰቃዩ፤ ጽ/ቤታቸው እየተዘጋና እየተዘረፈ፤ የመናገር፣ ሃሳብን የመግለጽ፣ የመጻፍና የማሰብ ድረስ መብታቸው በግልጽ እየተነፈገ ማነው ቅድመ ሁኔታ ማስቀመት የነበረበት?

ድርድርና ዕርቅ የህወሃት/ኢህአዴግ የሰሞኑ ዜማዎች የሆኑት ለምንድነው? ለኢትዮጵያ ሕዝብ ስለታሰበለት ነው? ህወሃት/ኢህአዴግ ለመሻሻል ስለፈለገ ነው? ይህ ከሆነ ሃሳቡ ሁሉን ነገር ትቶ ሚዲያውንና ምርጫ ቦርድን ብቻ ነጻ ያድርግ! ይልቅ ጉዳዩ ያለው ሌላ ቦታ ነው – ህወሃት በአንጋሽ ጌቶቹ ግልምጫ ስለደረሰበት ነው፡፡ እነርሱም ለኢትዮጵያ ሕዝብ አስበው ባይሆንም ህወሃትን ግን ክፉኛ ስላስደነገጠውና የወደፊቱ አልጨበጥ ስላለው “ዕርቅ፣ ዕርቅ፤ ድርድር፤ ድርድር” እንዲል አስገድዶታል፡፡

ለመሆኑ ዕርቅን እንዴት እንገልጸዋለን? የቀድሞዋ የፊሊፒንስ ፕሬዚዳንት ኮራዞን አኩዊኖ በጥሩ መልኩ ስለገለጹት የእርሳቸውን እንዋስ፤ እንዲህ ነበር ያሉት፤ “ዕርቅ ከፍትሕ ጋር መታጀብ አለበት አለበለዚያ ዘላቂ አይሆንም፡፡ ሁላችንም ስለ ሰላም ተስፋ ስናደርግ ሰላም በምንም መልኩ ይምጣ ማለት የለብንም፤ ነገር ግን በመርህና በፍትሕ ላይ የተመሠረተ መሆን አለበት፡፡” የህወሃት/ኢህአዴግ የዕርቅ ሃሳብ ከዚህ እውነታ ፍጹም የራቀ ነው፤ ፍትሕ አልባ፤ እውነት አልባ፤ ግልጽነት አልባ – የግፍ ዕርቅ ነው! ይህ ደግሞ ዕርቅ ሊባል ፈጽሞ አይችልም፡፡

ዜጎችን ላለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ከመግደል እስከ ማሰቃየት ተሰምቶ የማይታወቅ ግፍ እንደፈለገ የፈጸመ፤ የልጇ አስከሬን ላይ ተቀመጪ ብሎ እናትን ያሰቃየ የወንበዴዎች ቡድን እንዴት ነው ራሱ የዕርቅ ሐዋሪያ ሆኖ፤ ራሱ የሚያዛቸውን ፓርቲዎች ለድርድር፤ ራሱ የሾማቸውን የሃይማኖት መሪዎች ለዕርቅ የሚጠራው? የሃይማኖት መሪዎችስ በየትኛው ቅዱስ መጽሐፍ የተጻፈ ዕርቅ ሊሰብኩ ነው ግፈኛ በጠራው ጉባዔ ላይ የህወሃት ሹም በከፈተውና በዘጋው ስብሰባ ስለ ዕርቅ የሚናገሩት? የተጻፈላቸውን ካላነበቡ በስተቀር በሚያስተምሩት መጽሐፍት ላይ የሚናገረው፤ ግፍ የተሰራበት ፈጣሪ አምላክ ራሱን ዝቅ አድርጎ በደል ከፈጸሙበት ጋር ሲታረቅ ነው የሚነበበው እንጂ እንደ ህወሃት/ኢህአዴግ የፈለገውን ግፍ ፈጽሞ ሲያበቃ ኑ ታረቁ እያለ ሲያስገድድ አይደለም፡፡

ዴዝሞንድ ቱቱ ይህንን ብለዋል፤ “እውነተኛ ዕርቅ ርካሽ አይደለም፤ ምክንቱም በይቅርታ ላይ የተመሠረተ ስለሆነ በጣም ውድ ነው፤ ይቅርታ በተራው ደግሞ በንሰሐ ላይ የተመሠረተ ነው፤ ይህ ደግሞ ለተሰራ ስህተት ዕውቅና በመስጠትና እውነትን ግልጽ በማድረግ ተግባር ላይ የተመሠረተ ነው፡፡”

እውነት ፍርጥርጥ ብሎ ሳይነገር ዕርቅ የለም! በእውነት አጋቢነት ፍትህና ዕርቅ በአደባባይ ጋብቻ ሲፈጽሙ ካልታየ በስተቀር ግፈኛውም ግፉን ይቀጥላል፤ ዕርቅም የግፈኛው ትርከት ሆኖ ይቀጥላል፡፡


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ®” አቋም ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Lusif says

    January 21, 2017 10:39 pm at 10:39 pm

    I do not care who or what that entity is, I always admire, that is consistent and loyal to its words and objectives. The ruling party has never asked for reconciliation or peace. It believes in its strength and peace can only be maintained through the barrel of the gun. Whenever the ruling party is faced with strong demands or some kind problems, it send out let us discuss invitation letters to opposition groups. The moment the opposition receive that letter, the leadership go on setting up an equation, which never get right, but that give time and space for the ruling party to breath freely, comfortably.
    So who is naive, ignorant, shortsighted? The ruling party wants to stay in power. It wants to control the economic resources. That is what it doing whether we like it or not. Look in every aspect. The ruling party is doing what takes. Look the so called opposition, let alone being strong, the opposition is not close to match up. When one compare the ratio, it is 1:70.
    That is what I said the ruling party deserves my administration. Equally and on the other hand, I despise myself and the likes for not standing firm and consistent, as a result losing the struggle.

    Reply
  2. Ezira says

    January 23, 2017 02:20 pm at 2:20 pm

    ትክክል ብላችኋል ጎልጉሎች። እውነትና ነጋት እያደር ይጠራል እንደተባለው ሁሉ ሃቅ ተደብቆ አይኖረም። እዉነቱ ይፍረጥረጥና እርቅ መጀመሪያ ከፈጣሪ ጋር ሲቀጥል ከራስ ጋር በሰተመጨረሻም ከህዝብ ጋር የሚደረግ እርቅ ብቻ ነው ራስን ነጻ የሚያውጣ እንጅ የ COMMAND POST ጋጋታ አይደለም አራት ነጥብ።

    Reply
  3. Ezira says

    January 23, 2017 02:31 pm at 2:31 pm

    ግሩም ርዕሰ አንቀጽ ብራቮ ጎልጉሎች!
    በርቱ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule