• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የድል ፍሬ ፀሐይ

December 1, 2014 09:22 am by Editor Leave a Comment

የሕይዎት ዋስትና ፤ የፍጥረቱ ሲሳይ

ሃሌታዊ ጀምበር ፤ ለዚህች ማሕሌታይ

የተስፋ ብርሃን ፤ የማለዳ ፀሐይ

የድል በረከቱ ፤ መከራን ገላጋይ

እፎይታን አስኮምኳኝ ፤ ሁሉንም አማላይ

ኧረ ምን ነው ቀረሽ ፤ እባክሽ ቶሎ ነይ፡፡

አዝርቱን ውርጭ መታው ፤ ቀረ እንደ ጫጨ

አውድማው ነጠፈ ፤ ዘር መክለፍት ተፈጨ

ሁሉም በቁር ጠፋ ፤ ውሽንፍሩ አፋጨ

ሕይዎት ያለው ፍጥረት ፤ በአጭሩ ተቀጨ

የማለዳ ፀሐይ ፤ ሕይዎት መታደያ

ምን ነው በአፍሪካ ፤ ምን ነው በኢትዮጵያ

ሌሊቱ ረዘመ ፤ ምንድነው ምክንያቱ

አትወጭም እንዴ! ፤ ገደለን ምኞቱ

የድል ፍሬ ፀሐይ ፤ የፍጥረት ሕይዎቱ

በነፍስ ድረሽልን ፤ ይንጋልን ሌሊቱ፡፡

ቁር የቀፈደደው ፤ ያስቀመጠው አስሮ

ልሳኑ የተያዘ ፤ የደረቀው ከሮ

በሙቀትሽ  ይንቃ ፤ ይፈታ ሞት ሽሮ

እንደባከነ አይሙት ፤ ቀን ከሌት ተባሮ

ፍጥረት ሕይዎት ያግኝ ፤ በረከት ከአዶናይ

የትግል ፍሬ ፀሐይ ፤ እባክሽ ቶሎ ነይ፡፡

ነፍስሽ ያለው ሁሉ ፤ አንቺ የሆንሽ ሕይዎቱ

ከክቡሩ የሰው ልጅ ፤ እስከ ሕዋሳቱ

ከእጽዋት አዝርእቱ ፤ እስከ አእዋፋቱ

ከእንስሳት ዓሣቱ ፤ እስከ አራዊቱ

አንችን ያግኝና ፤ ይስመር የምኞቱ

ቀየው ጥጋብ ይሁን ፤ እፎይታን ያሽቱ፡፡

ሌሊቱ እረዘመ ፤ ሰው ተስፋ ቆረጠ

አንቺን መበጠበቅ ፤ ቀረ እንዳንጋጠጠ

ይህ ድቅድቅ ጨለማ ፤ የአጋንንቱ አሽከላ

ስንት ከዋክብት ዋጠ ፤ ስንት ሻማ በላ

እንችን እንዳያነጉ ፤ ወዲያ እንዳይከላ፡፡

ተስፋ ነጥፎ ጠፋ ፤ ትውልዱ ታበጠ

መተሽ ነፍስ ዝሪበት ፤ ያንችን ቀን ቋመጠ

ስትዘገይበት ፤ ተስፋ እየቆረጠ

ጨለማን ለመሸሽ ፤ ሁሉም ፈረጠጠ

እግሩ ወዳመራው ፤ ሔደ ሸመጠጠ

ሀገር እየጣለ ፤ ራሱን እየሸጠ

የደም መለያውን ፤ ከድቶ እየለወጠ

ሀገር ወና ቀረች ፤ ውድማው አረጠ

ሁሉም ባዶ ሆነ ፤ ባዶነት ፈጠጠ

አድባር ውቃቤ (ዐቃቤ) አጣ ፤ ቀልብ ደነገጠ

የድል ፍሬ ፀሐይ ፤ የፍጥረት ሕይዎቱ

የማለዳ ፀሐይ ፤ አንቺ አማላይቱ

በነፍስ ድረሽልን ፤ ይንጋልን ሌሊቱ፡፡

ጅቡ ይብላኝ እንጅ ፤ ጥርሱን እያፋጨ

ዐይኔን ወደ ምሥራቅ ፤ ሌሊቱን አፍጥጨ

አንችን እጠብቃለሁ ፤ ጨክኘ ቆርጨ

በአጋንንት ጥቃት ፤ ነፍሴን አስደንግጨ

ወደ ቤት አልገባም ፤ በፍርሐት ፈርጥጨ

ጉልበቴን አጽንቸ ፤ ፍርሐቴን ውጨ

እጠብቅሻለሁ ፤ ሞትን ተጋፍጨ

ተስፋ ላልቆረጠ ፤ በእምነት ለጸና

ምኞቱ ይሠምራል ፤ ቃሉም ይላልና

የጽናቴን ዳር ጫፍ ፤ ከጎሕ ሳላገናኝ

በፍጹም አልገባም ፤ መኝታም አልመኝ

ከቅጽበት የኋላ ፤ ሲደርስ መጨረሻው

ሊነጋ ሲል ሲከብድ ፤ ያ ድቅድቅ ጨለማው

አዎ ሊነጋ ሲል ፤ ጨለማው ግን ሳይገፍ

እሳት የመሰለ ፤ የሰሌዳሽን ጫፍ

ሳላይ ሳላረጋግጥ ፤ የመውጣትሽን ዜና

በጭራሽ አልገባም ፤ ምን ጻዕር ቢጠና

ገብተህ የተኛኸው ፤ ተስፋ ቆርጠህ በኛ

ጨለማን ሳትፈራ ፤ የጋኔን መጋኛ

የአራዊቱን ፉጨት ፤ ያበጠውን ሻኛ

ውጣ ተቀበላት ፤ ጥራት እንድትወጣ

ትንቢቱ እንዲፈጸም ፤ ያ ቀን እንዲመጣ፡፡

ጨለማ የሚያስፈራው ፤ ሰይጤ የሚጥል ገሎ

ብቻ ሲያገኝ ነው ፤ ያለን ተነጣጥሎ

ቆርጠህ ብትወጣ ፤ በመስክ በጎዳና

ሆ ብለህ በአንድነት ፤ ሸንጦህ ፍነና

ጨለማም ጋኔንም ፤ ኃይላቸው ይወድቅና

ጀምበር ትወጣለች ፤ ይዛ የተስፋ ፋና፡፡

እናም ውጣ ውጣ ፤ ስማ አንተም አሰማ

የአውሬ ሲሳይ ሳትሆን ፤ ሳይውጥህ ጨለማ

ሀገርህ ነግቶላት ፤ ወግ ደርሷት እማማ

በቀናው መንገድ ላይ ፤ ተደላድላ ቆማ

ሳታያት እንዳትቀር ፤ ዳኛ ተሠይማ

ውጣ ውጣ ውጣ ፤ ይህ ነው ያደራ ዓላማ፡፡

ኅዳር 21 2007ዓ.ም.

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule