• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሌቦ ነይ …

September 18, 2015 10:45 am by Editor 2 Comments

ማስታወሻ፤ ከጥቂት ሳምንታት በፊት አንድ የህወሃት አባል ወይም ተላላኪ እንደሆነ የታሰበ ግለሰብ 5 ሚሊዮን የእንግሊዝ ፓውንድ የሚገመት (በፎቶው እንደሚታየው) ጥሬ ገንዘብና ወርቅ በሻንጣው ይዞ ከኢትዮጵያ ወደ ለንደን እንግሊዝ ሲገባ ጋትዊክ አየር ማረፊያ ላይ በፖሊሶች ተይዟል። ግለሰቡ ለመጀመሪያ የፍርድ ምርመራ ፍርድ ቤት በቀረበ ጊዜ ዳኛው “ይህን ያክል ገንዘብ እንዴት በሻንጣ ልትይዝ ቻልክ?” የሚል ጥያቄ ሲያቀርቡ፣ ግለሰቡ “ገንዘቡ የመንግስት መሆኑንና ለመንግስት ስራ ለማዋል መያዙን” ገልጾዋል። ይሁን እንጂ ዳኛው “ይህን ያህል ገንዘብ በሻንጣህ የያዝከው በአገራችሁ ባንክ ስለሌለ ነው እንዴ?” በማለት ጥያቄ አቅርበዋል። ግለሰቡ ለጊዜው በዋስ የተፈታ ሲሆን፣ መስከረም ላይ በድጋሚ እንደሚቀርብ ተነግሯል። የወለላዬ ግጥም በዚህ ዘረፋ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ (ቅርብ የሆናችሁ ግጥሙን ጸረ ሙስና ኮሚሽን ለሚባለው አድርሱልን)

ኦሆሆ ሌቦ ነይ …
ኦሆሆ ሌቦ ነይ …

ይቺ አመለ ክፉ – መስረቅ የለመደች
ኦሆሆ ሌቦ ነይ …

አንድ ሻንጣ ሙሉ – ገንዘብ ይዛ ሄደች
ኦሆሆ ሌቦ ነይ …

ሰው ሀገር ቢገቡ – ከሀገር ቢሰርቁ
ብሩም አይበላ – አያደምቅም ወርቁ
ኦሆሆ ሌቦ ነይ …

እንኳንስ ከሀገር – ሰርቶም በውጪ ሀገር
ማንም አላገኘ – የያዙብሽን ብር
ኦሆሆ ሌቦ ነይ …

ህዝቡን አስርበሽው – ሰብስበሽ ሰብስበሽ
ዛሬ ሻንጣ ሙሉ – ለፖሊስ አስረከብሽ
ገንዘብ ብታገኚ ሀብት ሲሞላሽ
ሁሉም ያንቺ ፖሊስ – መስሎ ተሰማሽ
ኦሆሆ ሌቦ ነይ …

የፖሊስ ያለህ አትሉም ወይ?
የዳኛ ያለህ አትሉም ወይ?
ለሻንጣ ሌባ ህግ የለም ወይ?
ለፍትህ ሌባ ህግ የለም ወይ?

ልትሄጂ እንዳይሆን – ፈጽሞ ጠቅለሽ
ይሄን ሁሉ – ገንዘብ የያዝሽው ጠቅጥቀሽ
የፎቁ ኪራይ ነው – ወይስ የሆቴሉ
ከምን አገኘሽው – ሌቦ ይሄን ሁሉ
ኦሆሆ ሌቦ ነይ …

በበረከት ሞት – በይ ልጠይቅሽ
በአባዱላ ሞት – በይ ልጠይቅሽ
በሳሞራ ሞት – በይ ልጠይቅሽ
ገንዘብ አሲዞ ማነው የላከሽ
ኦሆሆ ሌቦ ነይ …

ሰብስበሽ ሰብስበሽ – ላትበይው ነገር
ተሸክመሽ ወስደሽ – በተንሽው ስው ሀገር
ለድሮውም ቢሆን – ታውቂበታለሽ ንግድ
ሀገሩ አገባሽው የሀገሩን ፓውንድ
ኦሆሆ ሌቦ ነይ …

የፖሊስ ያለህ አትሉም ወይ?
የዳኛ ያለህ አትሉም ወይ?
ለሻንጣ ሌባ ህግ የለም ወይ?
ለፍትህ ሌባ ህግ የለም ወይ?
ኦሆሆ ሌቦ ነይ …

ይሄን ሁሉ ገንዘብ – ማውጣትሽ ሰብስቦ
እስቲ ምን ይባላል – ወገንሽ ተርቦ
ዳኝነትን ሽረሽ – ህጉን አጥፍተሽው
ህዝቡን እያጋደልሽ – እርሙን አበላሽው
ኦሆሆ ሌቦ ነይ …

ገድለሽ ገድለሽ ጥለሽ – በየቦታው ስዉን
ሌቦ ከሬሳው ላይ- ዘረፍሽው ገንዘቡን
ባታይው ነው ሌቦ – አይንና ጥርስሽን
የኋላ የኋላ – አታጭም የጅሽን

ኦሆሆ ሌቦ ነይ …

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Gilentufagonji says

    September 25, 2015 12:33 pm at 12:33 pm

    Looting and stealing is not strange for tplf members because they have heirted from their grand parents who were been serving the italian invaders in Ethiopia

    Reply
  2. Gilentufagonji says

    September 25, 2015 12:42 pm at 12:42 pm

    Woyane has looted billion dollars from Ethiopia what they don’t understand is finally the money will return home and they will come to the peoples court

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule