• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዲያስጶራዎቻችን

November 30, 2016 06:55 am by Editor 1 Comment

ዲያስፖራ (ዲያስጶራ) የሚለው ቃል ትርጉም ‹‹ብትን /የተበተነ›› ወይም በአጪር አነጋገር ከትውልድ አገሩ ውጭ ተበታትኖ ያለ ሕዝብ ማለት ነው፡፡ በዚህ ትርጓሜ ከኢትዮጵያ መቶ ሜትርም ይሁን አንድ ሺሕ ማይል ይራቅ ከድንበር ማዶ ያለ ሁሉ ዲያስፖራ ነው፡፡ የምንገኝበት አገር፣ የትምህርት ደረጃችን፣ የወጣንበት መንገድ፣ ሃይማኖታችን ወይም ብሔራችን ዲያስፖራ ከመሆን (ከመበትን) አያድነንም፡፡ ስለዚህ አንድ ሰው በአውሮፕላንም ይሁን በመርከብ፣ ጥገኝነት ጠይቆም ይሁን አግብቶ፣ ፊደል የቆጠረም ይሁን ፕሮፌሰር የሆነ፣ እስላምም ይሁን ክርስቲያን፣ ዐማራም ይሁን ኦሮሞ ወይም ጉራጌ ወይም ሌላ ከድንበር ወጥተን ወደ ሌላ ሉዓላዊ አገር ከገባን ተበትነናል ማለት ነው፡፡ የምንገኝበት አገርም መመዘኛ አይደለም፡፡ አፍሪካ፣ አውሮፓ፣ አሜሪካ፣ ኤዥያ ወይም ኦሽኒያ መሆናችን ምንም ልዩነት አያመጣም፡፡ አንድ ሰው አሥመራ፣ ናይሮቢ፣ ካይሮ፣ ዱባይ፣ ፓሪስ፣ ዲሲ፣ ሲድኒ ወይም አንድ የዓለማችን ከተማ ላይ ቢሆን ከኢትዮጵያ ተነቅሏል፤ ተበትኗል፤ ልዩነት የለውም፡፡ አፍሪካ የሚኖር ጀግና ወይም አሜሪካ የሚኖር ደፋር የሚያስብል መስፈርትም የለም፡፡ በእኛ አገር ዲያስፖራ መሆንን እንደ ምርቃት (ጥሩ እድል) የመቁጠር እሳቤ አለ፡፡ ከአገር ወጥቶ መበተን እርግመት ወይም ምርቃት ነው የሚለውን ለጊዜው እንተወውና ስለብትኑ ማኅበረሰባችን ፖለቲካ ትንሽ እንበል፡፡

ብትን ወገን (ዲያስፖራ) በፖለቲካው ረገድ እስካሁን የተዋጣለት ሥራ የሠሩት የኢዝራኤል ዲያስፖራዎች ናቸው፡፡ ኢዝራኤል የምትባለዋ አገር የተመሠረተችው በዲያስፖራዎች ነው፡፡ ለነገሩ አይሁዶች ከአገራቸው ሲርቁ የበለጠ ስለአገራቸው የሚያስጨንቅ ነገር አላቸው፡፡ ቀድም ባሉ በብሉይ ዘመናት ዮሴፍ በወድሞቹ ተሸጦ ወደ ግብጽ አገር በተሰደደ ጊዜ ለወገኖቹ የሚሆን ጥሪት ያጠራቅም እንደነበር ማስታወስ ይቻላል፤ ሙሴም ቢሆን ጊዜው ከመርዘሙ ውጭ የተበተኑ ወገኖቹን ወደ አገሩ መልሷል፡፡ 

የእኛ አገር የዲያስፖራ ማኅበረሰብ ከቁጥሩ አንጻር ካየነው ከዚህ ግባ የሚባል ለአገር ፋይዳ ያለው ውጤት እስካሁን ማምጣት አልቻለም፡፡ ያ ማለት ግን አይችልም ማለት አይደለም፡፡ በዲያስፖራው ማኅበረሰብ ያሉ የአንዳንድ ችግሮች ከተስተካከሉ ለውጥ ማምጣት የማይቻልበት ምንም ዓይነት ምክንያት አይኖርም፡፡ የዲያስፖራው ማኅበረሰብ በሰለጠነ አገር እየኖረ የሰለጠነ የውይይት ባሕል ማዳበር ከፍተኛ ችግር ይታይበታል፡፡ በዚህ ምስኪን ብትን ማኅበሰረብ ውስጥ በርካታ ውስብስብ ችግሮች ቢኖሩም ወደ ዲሞክራሲ የሚደረገውን የአገር ቤት ትግል ውጭ ባለው ጥገኛ እንዲሆን የተደከመው ድካም እና ዐማራውን ሕዝብ ‹‹በአንድነት ኃይልነት›› መድቦ ማሞኘት ሕዝባችን ከባድ ዋጋ እያስከፈለው ነው፡፡ በውጭ አገር የሚገኙ ድርጅቶችና ማኅበራት (ከአፍሪካ እስከ አውሮፓና አሜሪካ) ከጥቂት ግለሰቦች የመኖሪያ መንገድ (Livelihood) ብሎም ግለሰባዊ ዝና (ፌም) ማግኛነት ወደ ትክክለኛ ዓላማቸው መመለስ ካልቻሉ ወደ ነጻነት የምናደርገው ጉዞ መራዘሙ አይቀርም፡፡ ጥይት በጮኸበት ቦታ ሁሉ ከእግዚአብሔር መላዕክ ቀድሞ መድረሱም ከባድ ዋጋ የሚያስከፍል ይመስለኛል፡፡

(ይህ አስተያየት የተሰጠው ጠቅለል ተደርጎ ለብዙዎች ድርጅቶች መሆኑ ልብ ይባል፤ የሰለጠነ ውይይት ለማድረግ የማትፈልጉ ሰዎች ከእኔ ጋ ጓደኝነታችሁ ያቆማል፤ ዝርዝር ጉዳዮችን ወደፊት ይዤ ለመምጣት እሞክራለሁ፤ እንደ ግለሰብ እንጅ እንደ ድርጅት አቋም የለኝም)

ምንጭ: Muluken Tesfaw Facebook


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Ezira says

    December 11, 2016 09:27 pm at 9:27 pm

    ሙሉቀን ተስፋው! አንተም “ዲያስፖራ” ከምትለው ኢትዮጵያዊ ከመቀላቀለህ በቀር በ25 ዓመቱ ኢህዴግን ለመቀየር ከሚደረገው ትገል አንፅር 25 ዓመት ብቅ ጥለም ካሉት ግለሶቦች የተለየህ አይደለህም። ዛሬ አንተም ጸጉረ ልዉጥ ከመሆንህ ዉጭ የምትገፋው ሃሳብ ፍራሽ አዳሽ ከመሆን አላለፈም። ብዙዎቹ አንተን መሰሎች ብቅ ከማለታቸው ደፍረታቸው “አስተማሪ” ሆነው መታበያቸው ነው። ከእነዚህ ዉሰጥ አንዱ በ 2005 /1997 መርጫ በኋላ ውደ “Dኢያስፕራነት” የተቀላቀለው “ወጣቱ” ጃዋር መሀመድ አንዱ ነው። ጃዋር ሙሃመድ ደግሞ በወጣት ምላሱ ማንነቱን ወዲያዉኑ ለብልቦ ያቃጠለ የ ዘማናችን “ፖለቲካ ተንታኝ” ነው። ፍየል ከመደረሱ ቅጠል መበጠሷ እንዲሉ ሙሉቀን ተሰፋዉና ጃዋአር መሃመድ በመሰምማማተም ይሁን ባለመሰማማት በሚዲያዊና ብበፌስ ቡኩ ኢንተርቪው ተደራጊ ጓዴኛሞች መሆናቸው በኮንኒስፓሪስ ቲዎሪ እይታ መሬት ላይ የሚታይ ሃቅ ነው። ተመሳሳይ ላባ ያላቸው ወፎች አብረው ይበራ! በርቱ እነ ሙሉቀን

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule