• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢሕአዴግ ቁልቁለት

May 31, 2015 06:33 am by Editor Leave a Comment

“ፋክት” መፅሔት ላይ ቋሚ አምደኛ በመሆን በየሳምንቱ በወቅታዊ ፖለቲካዊ አጀንዳዎች ዙሪያ የሚያተኩሩ ፅሁፎችን ወደ አንባቢ ሲያደርስ የነበረው ሙሉዓለም ገ/መድኅን አዲስ መጽሐፍ ለኅትመት አብቅቷል፡፡

የመፅሃፉ ርዕስ፡- የኢሕአዴግ ቁልቁለት

ደራሲ ፡- ሙሉዓለም ገ/መድህን

የገፅ ብዛት፡- 235

ዋጋ ለአገር ውስጥ፡- 52 ብር ለውጪ አገር፡- 20 ዶላር

አጠቃላይ ይዘት

መፅሃፉ በአራት ክፍሎች እና በአስራ አራት ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን፣ ክፍል አንድ ላይ “ቁልቁለቱን በኢሕአዴግ ጎዳና” በሚል አምስት ምዕራፎች ተካተዋል፡፡ በዚህ ክፍል ብሶት ወለደኝ የሚለው ህወሓት ተነሳሁለት የሚለውን የትግል ዓላማ እንዴት እየቀለበሰው እንደመጣ በዝርዝር ያስቃኛል፣ በመስመር መሀል ከጫካ ጀምሮ የህወሓት የፖለቲካ አሽከር ስለሆነው ኢህዴን/ብአዴን ፖለቲካዊ ክሽፈት ያነሳል፣ ለቁጥር ብቻ ስለሚፈልጉት የኢሕአዴግ ሴቶች የፖለቲካ መሪነት ተሳትፎ ከአህዛዊ መረጃዎች ጋር እያነፃፀረ የሴቶቹን የቁጥር ማሟያነት በማሳያዎች አስደግፎ ያብራራል፣ ስለ ተጨፈለቀው የዳኝነት ነፃነት ጥያቄ እና ፍሬን አልባ ስለሆነው የአገዛዙ የዴሞክራሲ ቁልቁልነት ይተነትናል ፣ የኢህአዴግ “አብዮታዊ ዲሞክራሲ” ኢትዮጵያን እንዴት ወደ ሶስተኛው አብዮት እየገፋት እንደሆነ በአገሪቱ የፖለቲካ አደባባይ ላይ እየታዩ ያሉ “አብዮታዊ ሁኔታዎች”ን እያጣቀሰ በዝርዝር ያስቃኛል፡፡

የመፅሃፉ ክፍል ሁለት ደግሞ “በአዙሪት የታጅበው የኢትዮጵያ ፖለቲካ እና የቁልቁለቱ ተፅዕኖ” በሚል የቀረበ ሲሆን፤ በዚህ ክፍል የተካተቱ ምዕራፎች የያዟቸው መልእክቶች የኢትዮጵያን ፖለቲካ ጥልፍልፋዊ ጉዞ ለማሳየት ተክሯል፡፡ በተለይም “የሦስት ትውልድ ተንከባላይ ዕዳ” በሚለው ምእራፍ ውስጥ ከነ ግርማሜ ንዋይ ትውልድ እስከ ያ ትውልድ ድረስ እንዲሁም ስለዚህኛው ትውልድ ተንከባላይ ዕዳ ማሳያዎችን በማንሳት በዝርዝር ለማብራራት ተሞክሯል፡፡

downward spiral of eprdfክፍል ሶስት የአገሪቱን የሰሜን ምዕራብ ማህበረ-ፖለቲካዊ ሁነቶች የሚያስቃኝ ሲሆን፤ በአካባቢው እየታዩ ያሉ የብሔርተኝነትና የጎጠኝነት ስሜቶች፣ የኢትዮ-ሱዳን የድንበር ጉዳይ፣ የአማራ ክልልና የትግራይ ክልል የአዋሳኝ ድንበር ወዝግብን በተመለከተ፣ በአካባቢው ስላለው ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር እና ስለ ቅማንት የማንነት ጥያቄና ውዝግቡ በዝርዝር ያስቃኛል፡፡

የመፅሃፉ የመጨረሻ ክፍል የሆነው ክፍል አራት “ቁልቁለቱን ለማቆም ትልቁ የቤት ስራችን” የሚል ሲሆን፤ በዚህ ክፍል አገሪቱ ካለፉት አራት አስርታት ወዲህ የተጓዘችበትን የማህበረ-ፖለቲካ ጉዞ በማስቃኘት መጪው ጊዜ እጅግ አስከፊ መሆኑን በማሳየት መአቱን ለመሻገር ተቀራርቦ መወያየቱና አቻቻይ የመፍትሔ ሀሳብ በማፍለቅ አገሪቱን በብሔራዊ እርቅ ማንፃት ምርጫ የሌለው መንገድ መሆኑን በስፋት ይተነትናል፡፡

ስርጭት

መፅሀፉን በአገር ቤት በዋናነት በአዲስ አበባ ብሔራዊ ቲያትር ጀርባ “አይናለም መፅሐፍት መደብር” እና ጃፋር መፅሃፍት መደብር ውስጥ በመሸጥ ላይ ይገኛል፡፡ መፅሃፉ ለጊዜው በሰሜን አሜሪካ ሜሪላንድ ግዛት ውስጥ ባሉ የኢትዮጵያን ሬስቶራንቶች እና የሐበሻ ሱፐር ማርኬቶች በ20 ዶላር የቀረበ ሲሆን፤ በቀጣይ ቋሚ የመሸጫና ማከፋፈያ ቦታ ለማመቻቸት ጥረት በመደረግ ላይ ነው፡፡ በሌሎች የሰሜን አሜሪካ ግዛቶች፣ ካናዳ፣ አውሮፓ፣ አውስትራሊያ፣ መካከለኛው ምስራቅ፣ ደቡብ አፍሪካና መሰል አገራት መፅሐፉን ለመሸጥ የሚቻልበትን ሁኔታ ለማመቻቸት የመፅሃፉን ዋና አከፋፋይ በስልክ ቁጥር 0918 19 19 43 በመደወል ማነጋገር ይቻላል፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule