• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የህወሃት አውሬነት፣ ከውልደት እስከ ህልፈት? ወይስ አገር “እስክትፈርስ”?

July 2, 2016 12:11 am by Editor 6 Comments

* ይብላኝ ለእናንተ ለአውሬው ቀንድና ግምባሮች!

ፈቃደኛ ስለመሆኑ ባደባባይ ባልተጠየቀው የትግራይ ህዝብ ስም ራሱን ተገንጣይ ብሎ ሰይሞ አገር የሚገዛው ህወሃት፣ ከቀን ወደ ቀን ግፍ እየመከረ ነው። በአገር ስም እስከ አፍንጫው በታጠቀው ጠመንጃና በዘረፈው ሃብት በመተማመን በያቅጣጫው ንጹሃንን እየጨፈጨፈ ነው። እስር ቤት አጉሮ  እያሰቃየ ነው። ያልፈጸመውና የማይፈጽመው ሰቆቃ የለም። ህጻን፣ አዋቂ፣ አዛውንት፣ እናት፣ አባት ሳይመርጥ የጥይት አረሩን እያወረደ በያይነቱ ደም እየተጋተ ነው። ቂም እየከመረ ነው። ከቀን ወደ ቀን ደምና ግፍ የሚበቃው አይመስልም። ወዳጆቹም ሆኑ በስማቸው የሚነገድባቸውም ተው ሲሉት አይሰሙም። ምን ይሁን? ይህ አውሬነት እስከመቼ ይቀጥላል?

“በጉልበት ትግሬ ተደረግን እንጂ ፍጥረታችን ትግሬ አይደለም” ያሉ ይገደላሉ፣ ይታፈናሉ፣ ይገረፋሉ፣ እርሻቸው ይነጠቃል፣ ከመኖሪያቸው ይፈናቀላሉ። “መሬታችን ለምን ይወሰደብናል” ያሉ የኦሮሞ ልጆች በጅምላ ይፈጃሉ። በጅምላ ታፍነው አሰቃቂ ሥቃይ ይደርስባቸዋል። ታፍነው የደረሱበት የማይታወቀውን ቤትና ወላድ ይቁጠራቸው፣ የጋምቤላን ለም ምድር ለመቸብቸብ ሲባል ምንም የማያውቁ ወገኖች ተፈጁ፣ ታሰሩ፣ ተፈናቀሉ፣ ኦጋዴን ውስጥ የተፈጸመው ለሰሚው ግራ የሚያጋባ ነው። አንድ ምስኪን እናትን አራት ቀን አስከሬን አሳቅፎ ማሰቃየት ምን ማለት ነው? ከዚህ በላይ አውሬነት ምን አለ?

በያቅጣጫው የሚሰማው ለቀሶ ነው። እመጫትን በዶፍ ዝናብ ከቤት አውጥቶ መጣል ምን ማለት ነው? ህጻናትን እየገደሉ ከራባት አንጠልጥሎ አፍ መክፈትና “ጅኒ” ብሎ መዘበት በምን መስፈርት ልክ ይሆናል? እስኪ አፍቃሪ ህወሃቶች ረጋ በሉና አስቡ። በኦሮሚያ የሚሆነውና የሆነው፣ አማራ ክልል እየተደረገ ያለው፣ ኦጋዴን የሚፈጸመወና የሚፈጸመው፣ በደቡብ ክልል የተለያዩ ወረዳዎች የሚታየውና የሚሰማው ግፍና በየአቅጣጫው የሚሰማው የእናቶች እንባ እንዴት እርካታ ይሰጣችኋል? እንዴት ደረታችሁን ያስነፋችኋል? ይህ ሁሉ በናንተ ቤተሰቦች ላይ ቢደርስ ትወዳላችሁ? ስለምን አውሬነትን ታበረታታላችሁ? ስለምንስ ግፍ በሚፈጸምባቸው ወገኖቻችሁ ላይ ትሳለቃላችሁ? ህወሃት ነጻ ያወጣችሁ ዘንድ ፍላጎታችሁ ከሆነ ሁሉ በጃችሁ ነውና ደሃውን ህዝብ ልቀቁት!! ሂዱ። አለያ ደግሞ ድሆች ሲገደሉ፣ ሲታሰሩ፣ ሲታፈኑና ለሥቃይ ግፍ ሲዳረጉ በግልጽ፤ በገሃድ፤ በአደባባይ ተቃወሙ። ፍትህን እመኑባት!!

ከቀን ወደ ቀን እየሆነ ያለው ሁሉ የሚዘገንን ነው። የሚቀፍ ነው። ብልሆች ሲናገሩ “ውሻን ወደ ቁልቁለት አታባር፣ ሲዞር ዳገት ይሆንብሃል” ይላሉ። አዎ! ዛሬ ህወሃት ዳገት ላይ ነው። ዳገት ላይ ሆኖ የሚድኽውን፣ የሚራመደውን፣ የሚሮጠውን፣ ደካማውን፣ ህጻናትን፣ ሁሉን በጅምላ እየነዳ ነው። እየደፋ ነው። ከድንቁርና ጋር የተቀላቀለ ጥጋብና ትዕቢት አሳውሮታል። ተግባሩ ስለሚያስደነብረው ተቃውሞን አይወድም። ካልተቃውሙት ወደብ ይሸልማል። አገር ቆረሶ ይሰጣል/ይሸጣል። ሰዎች ለመብታቸው ሲነሱ መልሱ የምናየው ነው። አውሬነት ነው። በዚህ አውሬነቱ ህወሃት በደም ተጫማልቋል። የደም እዳ በዝቶበታል። አውሬነቱ ማብቂያ የሌለው ህወሃት ሰሞኑን በአቶ ሃብታሙ ላይ የፈጸመውና እየፈጸመ ያለው ተግባሩ ይህንኑ አውሬነቱን ያረጋገጠ ይሆናል።

አቶ ሃብታሙ ህወሃት አጥብቆ የሚጠላው ወጣት ፖለቲከኛ ነው። በፈጠራ ክስ አሰረው። እስር ቤት አማቅቆ፣ አሰቃይቶ በመጨረሻ “ነጻ” አለው። ተመልሶ ይግባኝ ተጠየቀበት። ከዛም ይግባኙ እንዳለ ሆኖ ተፈታ። አሁን ስለሚያሰቃየው ህመም ለህብር ሬዲዮ ሲያስረዳ ታሪኩ የሚያስለቅስ ነበር። አንድ መጸዳጃ በሌለበት ክፍል ውስጥ እንዴት ያሳልፍ እንደነበር እዚህ መዘርዘሩ ባያስፈልግም ህሊና ላላቸው ሁሉ /ከአውሬዎች በቀር/ የሚያም ነው። እንግዲህ ራሱ ህወሃት በፍርድ ቤት በኩል እንዳመነው አቶ ሃብታሙ የታሰረው ያለ በቂ ማስረጃ ነበር። አፍቃሪ ህወሃቶች እስቲ አስቡት! አቶ ሃብታሙ አያሳዝንም?! ይህ ሁሉ ሳያንሰው ታይላንድ ወይም ሌላ አገር ሄዶ የመታከም መብቱ ሲገፈፍ … ሰውየው ቀብር ሄዶ ሲያለቀስ “ባክህ በቃህ” ሲሉት “ተዉኝ ለራሴ ነው የማለቅሰው” አለ እንዲሉ፣ ነግ በእኔ ነውና እንዲህ ያለ አውሬነትን መቃወም ግድ ነው።

ጎልጉል አቶ መለስ ሲሞቱ ከበሮ አልመታችም። እንደ ሰው ሞታቸው አሳዝኖናል። ነገር ግን በሰሩት የአውሬ ተግባር ህግ ፊት እንዲቀርቡ እንመኝ ስለነበር ፍርድን በሞት ማምለጣቸው አናድዶናል። እንደ ዝግጅት ክፍላችን እምነት መለስን ማስነሳት የሚቻል ቢሆን ትውልድ ሁሉ እንዲማርበት ፍትሕ ሲበይንባቸው እንዲያይ ከሞቱበት ይነሱ ዘንድ የሚፈለገውን ሁሉ እናደርግ ነበር።

እናም አቶ ሃብታሙ ዶላር አልጠየ፣ አሳከሙኝ አላለ፣ ሃኪም ቢያዝ ባያዝ፤ ቢፈቅድ ባይፈቅድ ውጪ ሃገር ሄዶ መታከም ከፈለገ እንዴት ይከለከላል? አሁን ይህንን አውሬነት አዳንቆና አወድሶ በየማህበራዊው ሚዲያዎች ማቅረብ ምን ይባላል? ያሳፍራል! ያሳዝናል! ወይስ የተፈራ ሌላ ነገር አለ? የእስሩ ግፍ ያደረሰበት የበሽታ ጉዳት እና መጠኑ ውጪ ሲወጣ በባለሙያዎች ያለጥርጥር እንዳይጋለጥ ተፈርቶ ይሆን?

ህወሃት ውስጥ የተካተቱ የሚስቶቻቸው ጥርስ ለማስሞላት፣ ልጆቻቸው ለሽርሽርና ለቶንሲል የውጪ ህክምና ተጠቃሚዎች በሆኑባት አገር … ባለስልጣናት ለወሲብ በሳምንት ሁለቴ የሚመላለሱባት ታይላንድ ብርቅ ሆና ህይወትን ለማዳን ደጇ ሲዘጋ … እንተወው!! ለሁሉም ህወሃት ተፈጥሮ ብዙም ሳይቆይ አውሬዎቹ መሪ ሆነው የወገኖቹን ደም እየጠጣ ተጓዘ። ተጉዞም እዚህ ደረሰ። አሁን በያዘው አኳኋን ደም የሚጠግብ አይመስልም። አውሬነቱንም እስከ ህልፈት ብሎ ምሏል። ወይም እሱ እንደሚመኘውና ሁሌም እንደሚያስፈራራው ኤርትራ ላይ መንግስት ለጥፎ ኢትዮጵያን እስኪያፈርስ በዚሁ አውሬነቱ ይቀጥላል። የሚያሳዝነው የአውሬ ቀንድና ሾከና ሆነው የሚያገለግሎት ባንዳዎች ናቸው። ለፍርፋሪ ተገዝተው አብሮ አደጋቸውን የሚያሳደዱት ከሃዲዎች። እኚህ ባንዳዎች ሲጣሉ የአውሬው ፈርስና እዳሪ መሆናቸውን እያዩ አለማመናቸው ይገረማል!! አዋቂዎች ሲያዝኑ “ይብላኝ ለእናንተ” እንዲሉ!!

ሕዝብን ሁልጊዜ ቁልቁለት እያባረሩ መግዛት አይቻልም፤ ሕዝብ ፊቱን ያዞረ ቀን፤ ቁልቁለቱ ዳገት ሲሆን፤ ተሳዳጁ አሳዳጅ ሲሆን፤ … ማን ይታደግ ይሆን?!


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ®” አቋም ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. gud says

    July 5, 2016 06:52 pm at 6:52 pm

    Answer from pro TPLF

    Is golgul a media or a political organization ?

    Ethiopia is a country of 100000000 people . Any
    Disturbance here and there is in avoidable .

    Finally , I urge Golgul to act as media !

    Reply
    • Editor says

      July 6, 2016 03:37 am at 3:37 am

      It depends how you define it. We are observing what you are posting for almost everything we are publishing. Unlike the the “terrorist organization” that you are tittle-tattling, scribbling and crying for daily, you have been given freedom to post what you believe on our media outlet. This defines who we are.

      Thanks for your “urge” but please pass that to the TPLF – because in the TPLF controlled Ethiopia neither the media nor political organizations practically function.

      And we “urge” you not to reply to this post.

      Editor

      Reply
  2. gud says

    July 5, 2016 06:53 pm at 6:53 pm

    Answer to your last paragraph

    Did u forget that no one was with us when we were butchered with your dada , and grand dada ?

    Reply
  3. gud says

    July 6, 2016 04:14 pm at 4:14 pm

    Editor
    Thanks for your reply .

    Please re visit your posts and you will learn how blind haters you r !

    You r no use for the current and future ethiopia .

    Reply
  4. Kebede says

    July 7, 2016 07:33 pm at 7:33 pm

    Nothing impressive. .like derg propoganda

    Reply
  5. Deribsa says

    July 8, 2016 08:01 am at 8:01 am

    Yap, they are fascists. I can explain why they have to be fascists for those tplfits. They are working towards their objective and any means is justifiable as long as it helps them to win. The Amhara, Oromo …. foot soldiers? you are practically burning your house while your children and family members are inside. When are you going to get it? How long do you think you can live in this world?
    How come you end up doing the dirty work for tplf? You are a disgrace to your family and community. To die clean is as great as to live with dignity. are you gonna to die as a foot soldier of this lowlife fascists? Think again!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule