• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አማራ የሚፈናቀለው ሆነ የሚገደለው በመንግስት ፍቃድ ነው!

May 17, 2018 06:44 am by Editor 1 Comment

ትላንት (May 15) በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል አበጥር ወርቁ በተባለ የአማራ ብሔር ተወላጅ ላይ የተፈፀመውን አሰቃቂ ግፍ ተመልክተናል፡፡ ይህ ከመሆኑ ከአንድ በፊት ደግሞ ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ከ527 በላይ አባወራዎች በድምሩ 2000 ከሚሆኑ ቤተሰቦቻቸው ተፈናቅለዋል፡፡

እነዚህ “ሕገ ወጥ ናችሁ” በሚል ሰበብ ተዘርፈውና ተደብድበው የተፈባቀሉት አማራዎች ህጋዊ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ያላቸው ናቸው፡፡ በባለቤትነት ለሚያስተዳድሩት መሬት በአግባቡ ግብር ይከፍላሉ! በፎቶው የሚታዩት የይዞታ ማረጋገጫ ደብተሮች ባህርዳር ጊዮርጊስ ቤተ ክርስትያን ተጠልለው የሚገኙ ሶስት አባውራዎች ናቸው።

እነዚህ ሰዎች ያለ ምንም መነሻ ምክንያት ከመሬታቸው አልተፈናቀሉም፣ በግፍ አልተገደሉም፡፡ ከዚህ በስተጀርባ በጥላቻና ማንአለብኝነት የናወዙ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የመንግስት ሃላፊዎች እጅ አለበት፡፡ ለምሳሌ ከላይ የተጠቀሱት አባወራዎች በሚያዚያ ወር መጀመሪያ ላይ ከመፈናቀላቸው በፊት ለምሳሌ የበሎ ዲዴሣ ቀበሌ ሃላፊ የሆነው አቶ ንጉሱ ጀርሞሣ በቀን 16/07/2010 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ መሠረት እስከ መጋቢት 30/2010 ዓ.ም በአከባቢው የሚኖሩ አማራዎች ንብረታቸውን ሸጠው ወይም ጥለው እንዲወጡ አዝዟል፡፡

በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የሚኖሩ አማራዎችን ያለ አግባብ እንዲፈናቀሉና እንዲገደሉ የሚያደርጉት እንደ አቶ ንጉሱ ያሉ የቀበሌ ሃላፊዎች አይደሉም፡፡ ከዚያ ይልቅ፣ በወረዳ፥ ዞን፥ ክልል፥ እንዲሁም በፌደራል ደረጃ የሚገኙ የመንግስት ሃላፊዎች እጅ አለበት፡፡ ከታች እስከ ላይ ያሉት የመንግስት ሃላፊዎች ለአማራ ህዝብ ባላቸው ሥር-የሰደደ ጥላቻ ምክንያት በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ አማራዎችን በማፈናቀልና በመግደል ተሳታፊ ባይሆኑ እንኳን አማራዎች ለሚያሰሙት ብሶትና ቅሬታ ግድየለሽ መሆናቸው እርግጥ ነው፡፡ ላለፉት 27 አመታት በኦሮሚያ፥ ደቡብ፥ ጋምቤላ፥ ትግራይ፥ እንዲሁም በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የአማራ ብሔር ተወላጆች ሲገደሉና ሲፈናቀሉ ማስቆም ይችሉ ነበር፡፡

ዛሬ ላይ ከ2000 በላይ አማራዎች ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የተፈናቀሉት፣ አበጥር ወርቁ በተባለው ግለሰብ ላይ አሰቃቂ ግፍ የተፈፀመው ትላንት ተመሣሣይ ድርጊት የፈፀሙ ሰዎች በህግ ቁጥጥር ስር ውለው የማያዳግም እርምጃ ባለመወሰዱ ነው፡፡ባለፈው የሚያዚያ ወር አማራዎች ከክልሉ የተፈናቀሉት መጋቢት ላይ የበሎ ዲዴሣ ቀበሌ ሃላፊ የሆነው አቶ ንጉሱ ጀርሞሣ በፖሊስ ለፍርድ ባለመቅረቡ ነው፡፡ አቶ ንጉሱ በአከባቢው የሚኖሩ አማራዎች እንዲፈናቀሉና እንዲገደሉ የሚያደርገውን ትዕዛዝ ያስተላለፈው የቤኒሻንጉል ግሙዝ ክልል የርዕሰ መስተዳደር እና የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ ለፍርድ ባለመቅረባቸው ነው፡፡

የቤኒሻንጉል ግሙዝ ክልል የርዕሰ መስተዳደር እና የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ የሆኑት አቶ ሰለሞን ጂሬኛ በዚህ አመት የጥቅምት ወር (እ.አ.አ በ04/03/2017 ዓ.ም ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ “የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት የትግራይ ክልል ተወላጆችን 600ሺህ ብር እና የአውሮፕላን ትኬት ሸፍኖ ልኳቸዋል”። በክልሉ የሚገኙ የአማራ ክልል ተወላጆች በተመለከተ ደግሞ “በሕገ ወጥ መንገድ የያዙት መሬት እንዲለቁና ወደ መጡበት ክልል እንዱመለሱ ተደርጓል” ብለው ነበር፡፡ ይህ የክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣን ህወሓት/ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ሲመጣ በደቡብ አፍሪካ የወደቀው የአፓርታይድ ስርዓት ዛሬም ድረስ ኢትዮጲያ ውስጥ በተግባር እንዳለ በመንግስት ሚዲያ ላይ በይፋ ተናግሮ ማንም ምንም አላለውም፡፡

አቶ ሰለሞን ጂሬኛ የቤኒሻንጉል ግሙዝ ክልል በአማራዎች ላይ ተግባራዊ ያደረገውን አድልዎና ግፍ በይፋ በራሱ አንደበት ያረጋገጠበት ምክንያት ምንድነው? አጭርና ግልፅ፣ መንግስታዊ ስርዓቱ በአማራ ህዝብ ላይ የፈለገውን አሰቃቂ ተግባር እንዲፈፅም ይፈቅድለታል፡፡ ምክንያቱም በህወሓት መሪነት የተዘረጋው መንግስታዊ ስርዓት ዓላማና ግቡ የአማራን ህዝብ መበቀል ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ “የአማራ የበላይነት፥ ነፍጠኛ፥ ትምክህተኛ፥ የድሮ ስርዓት ናፋቂ፥…” እያለ በአማራ ህዝብ ላይ ዘወትር ጥላቻ ይሰብካል፡፡

በዚህ መሠረት በቂም-በቀል የታወሩ ሰዎች በኦሮሚያ፥ ደቡብ፥ ጋምቤላ፥ ትግራይና ቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልሎች በሚገኙ አማራዎች ላይ በማንአለብኝነት አሰቃቂ ግፍና በደል ሲፈፀሙ በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የመንግስት ሃላፊዎች ነገሩን በቸልታና ግድየለሽነት እንዳልሰማ-እንዳላየ ሆነው ያልፉታል፡፡ በመሆኑም በአማራ ህዝብ ላይ አሰቃቂ በደልና ግፍ እንዲፈፀም በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ ፈቅደዋል፡፡ በአጠቃላይ የአማራ ህዝብ የሚፈናቀለው ሆነ የሚገደለው በመንግስት ፍቃድ ነው!

ስዩም ተሾመ

ምንጭ፤ Ethiopian Think Thank Group by Seyoum Teshome

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: abiy, amhara, andm, Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Eunetu Yeneger says

    May 24, 2018 05:34 pm at 5:34 pm

    ሰው ከመሆን ደረጃ ለምን ወደ ዘር ወርድን?
    የትኛው ይቀድማል?ሰውነት ወይስ ትግሬነት/ኦሮሞነት አማራነት/ሃድያነት/ ወዘተ?

    የአማራ ሕዝብ መከራ ምንጩ በእውነት ምንድነው?
    መከራ ያበዙበትን እነዚህን ሰዎች በእውነት ምን አድርጓቸው ነው?
    በእውነት አማራ በአማራነቱ በትግራይ፣ በኦሮሞና በሌሎች ላይ የሠራው ግፍ አለ?
    አማራና አማርኛ ለምን በራሳችን ወገኖች ተጠላ?

    የሰማሁትን እንካችሁ፡

    1)አንድ የኤርትራ ሕጻን ስታድግ ምን መሆን ትሻለህ ሲባል
    የጦር አውሮፕላን አብራሪ! ለምን እሱን ሥራ መረጥክ?
    ኢትዮጵያያን ለመደብደብ ብሎ እርፍ!
    በወላጆቹና በሰፈሩ ቂመኛ ሰዎች ሲባል የሰማውን!!

    2) አንድ ለጋብቻ የደረሰ እውነተኛ የክርስቶስ ተከታይ፡
    አብራው ቤ/ክ የምታመልክን የወለጋ ወጣት ሴት
    ለጋብቻ ከልቡ በእውነት ይጠይቃታል፤
    አንተን በፍጹም አላገባሃም ብላው እርፍ!
    ምነው???? ሲላት
    አማራ ስለሆንክ ነው።
    /ኢሕአዴግ በገባ ከ3 ዓመት በኋላ የተፈጸመ እውነት/

    ከዚህ የበለጠ ከሰውነት ደረጃ መውረድ ምን አለ????
    ኧረ እናስተውል???ምነው ሰው ሰው መሆኑን እረሳ??

    ልጄ ሰለሞን ሆይ!
    ሰው ሁን!!!
    /1ኛ ነገሥት 2፡1-4/

    Therefore, are we really CHRISTIAN ?????

    Eunteu Yeneger

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule