• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የ11ኛው ሰዓት አዋጅ እና ሕዝብ

October 10, 2016 09:16 am by Editor Leave a Comment

ስለ አስቸኳይ ግዜ አዋጁ የጠየቅኩት አንድ የአዲስ አበባ ወጣት ምላሽ አስገረመኝ። “የምን አዋጅ?” ነበር ያለው።

“ትላንት የታወጀው።”

“አቦ መስሚያችን ጥጥ ነው። … ሚሰማ የለም” አለኝ።

ሃይለማርያም ደሳለኝ ዝም ብለው ኖሯል የደከሙት!

“ለመኖር ብቸኛው አማራጭ ሌላው እንዲኖር መፍቀድ ነው።” ብለው ነበር የህንዷ ማህተመ ጋንዲ። እነሱ እየኖሩ ሌላው እንዳይኖር ለሚሹ ራስ ወዳዶች ትልቅ መልእክት ነበረው። ማስተዋል የተሳናቸው ግን “እኛ ብቻ እንኑር” ይህንን የማይቀበል በሙሉ ይጥፋ የሚለውን ጭፍን አመለካከት እንደ ብቸኛ ምርጫ ይዘውታል።

ይህ የ11ኛው ሰዓት አዋጅ “አለሁ፤ አልሞትኩም” ለማለት ካከልሆነ በስተቀር ምንም የሚያመጣው ለውጥ እንደማይኖረው እንገነዘባለን። አንድ በነፍስ ዉጪ፤ ነፍስ ግቢ ሁኔታ ያለ አካል ከገባበት የፖሊቲካና ወታደራዊ አጣብቂኝ ዉስጥ ለመዉጣት መፍጨርጨሩ ግድ ነው። በመጨረሻ በራሳቸው ሰንሰለት ተጠፍረው ከዚያ እስር ለመውጣት የሚወስዱት እርምጃ  አጣብቂኝ ውስጥ አሰመጣቸውና በአጭሩ የተነፈሱበት ንግግር ነው። ከዚያ አያልፍም።

አዋጁ የሚገድባቸው መብቶች እና የሚያከናውናቸው ተግባራት ገና በዝርዝር ይፋ አልሆኑም። ግን ተግባሩ ከአዋጁ በረጅም ርቀት ቀድሟል። ሰራዊቱ ህዝቡን እንዲያረጋጋ ሳይሆን ይልቁንም ሰላማዊ ሰልፈኛው ላይ ማንኛውንም የሃይል እርምጃ እንዲወስድ ትእዛዝ ከተሰጠ አንድ ወር አልፎታል።

በቅርቡ በቱርክ እንደተደረገው – አለም አቀፍ ህግ ያሰፈራቸውን የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች ለመጣስ አንባገነን መንግስታት የሚጠቀሙበት መሳርያ ነው – አስቸኳይ ግዜ አዋጅ። እኛ ጋ ግን እነዚህ ድንጋጌዎች አንጻራዊ ሰላም በነበረበት ግዜ እንኳን አላየናቸውም። አዋጁ ወጣም አልወጣ አሁን ባለው ውጥንቅት እና በፖለቲካ አየሩ ላይ የሚያመጣው ለውጥ አይታይም። የጅምላ ግድያውን ሕጋዊ ሽፋን ሰጡትም አልሰጡት ዘር ከማጥፋት እና ሰብአዊነት ላይ ከሚፈጽሙት ወንጀል ራሳቸውን አያነጹም።  ችግሩ ከእጅ ወጥቷል።

ከፍተኛ ስጋት ላይ ጥሏቸው የነበረው የማህበራዊ ሜዲያው ነበር። ከቁጥጥር ውጭ የሆነውን ይህንን ጉዳይ እየዘጉ መክፈቱ በምእራቡ አለም አስወቀሳቸው እንጂ እነሱ እንዳሰቡት አንዳች አልፈየደም። ኢንተርኔትን ጨርሶ ለመዝጋትና ለዚህም ሕጋዊ ሽፋን መስጠት ተብሎ ይጠቅም ይሆናል ይህ አዋጅ። “ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማንኛውንም ዓይነት የመገናኛ ዘዴ የመዝጋት ስልጣን አለው!” ብለውናል። አስተዋይ ቢሆኑ ኖሮ ከስልክ እና ከኢንተርኔት  ይልቅ ህዝብ ላይ የደቀኑትን አፈሙዝ ነበር መዝጋት!

አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን የአዋጁን ዜና ሲዘግቡ “ተቃውሞውን ለማስቆም”  ብለውታል። 100 ፐርሰንት የመረጣቸው ሰው ላይ እንዲህ አይነት አዋጅ ለምን እንዳወጡ የሚጠይቅ ግን የለም። በጥይት እና በመርዝ ጭስ ያልቆመው አመጽ እንዴት ሆኖ በአዋጅ ይቆማል የሚልም አልተገኘም?… አዋጅማ ተለመደ። ሕወሃቶች ጥርሳቸውን የነቀሉበት ጉዳይ ነው። “አስቸኳይ” የሚለው ሃረግ ከፊቱ ገባበት እንጂ ሃገሪቷ ላለፉት ሁለት አስርተ-አመታት በህግ ሳይሆን በአዋጅ ነው እየተገዛች ያለችው። የፕሬስ አዋጅ፣ የጸረ-ሙስና አዋጅ፣ የጸረ ሽብር አዋጅ፣ የግብረሰናይ ተቋማትን የሚያግድ አዋጅ፣ … የሰው ልጅ መብት በሙሉ እነሱ በሕዝብ በሚጭንዋቸው አዋጆች ታስረዋል። ይህንን አዋጅ ከሌሎቹ አዋጆች የሚለየው ሃይለማርያም ደሳለኝ በቴሌቭዥን ወጥተው ምጥ እንደያዛት ሴት አዋጁን መንበባቸው ብቻ ነው።

አረፋፍዶ የተነገረው ይህ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ የኢትዮጵያ ሕዝብ አልሰማውም። ሕዝቡ የህወሃት ፕሮፓጋንዳ ጣብያዎችን ከዘጋ ሰነባበተ። በማህበራዊ ሜዲያ እንዳይሰማው የኢንተርኔት አገልግሎቱን ቆርጦታል። አዋጁ ለማን እንደተነገረ ግልጽ አይደለም።

እንደማንኛውም አንባገነን ገዥ እነሱም ዘላለም እንቆያለን ብለው ያስቡ ነበር። ግና ነገሮች ሁሉ ፈጠኑ።  ሕዝብ በረጅም ቀደማቸው።እጃቸው ላይ የህዝብ ሃብት እና ደም አለ። ከዚህ አምልጦ ለመውጣት ግዜ መግዛት ግድ ነው። አንድም ቀን ዕድሜ ነው ይላሉ አበው። ግዜ እንደ ጉቶ ሲያጥርባቸው፣ ትንሽ ግዜ ለመግዛት መፍጨርጨር ግድ ነው። ሰአታቸው አልቆ በባከነች ደቂቃ ውስጥ እንዳሉ ተገንዝበዋል። ግን ስልጣን ለመልቀቅም ሆነ ሃገር ጥሎ ለመጥፋት አልተዘጋጁም። በራሳቸው ሰንሰለት ተጠፍረው ከዚያ እስር ለመውጣት የሚያደርጉ አጣብቂኝ ሁለት አማራጭ ሲኖር ለምርጫ የሚከብድ አጣብቂኝ ይኖራል።

እንደዚህኛው ጫን ያለው ባይሆንም ምርጫ 97 ወቅትም ተመሳሳይ አዋጅ ወጥቶ ነበር። ሟች ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ በቴሌቨዥን ቀርበው የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግና ሌሎች ተያያዥ መብቶች ለአንድ ወር የተገደቡ መሆናቸውን ተናገሩ። ይህንን እና አዲሱን አዋጅ የሚያመሳስላቸው አንድ ነገር አለ። ሁለቱም ራሳቸው ያወጡትን ህገ-መንግስት የሚጥሱ ህገ-ወጥ አዋጆች ናቸው። ሀገሪቱን እያስተዳደርን ያለንበት የሚሉት ህገ-መንግስት በአንቀጽ 93 ያሰፈረውን ድንጋጌ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚታወጀው ውጭ ወረራ አልያም የተፈጥሮ አደጋ ሲያጋጥም ወይም የሕዝብን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል በሽታ ሲከሰት  በሚኒስትሮች ምክር ቤት ተደንግጎ በምክር ቤቱ ተቀባይነት ካገኘ በኝላ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሁለት ሦስተኛ ድምጽ ሲጸድቅ ነው።

ከህዝብ ጋር እየተላተሙ ወደማይፈታ ችግር ውስጥ ራሳቸውን እየዘፈቁ ሽንፈትን ሲከናነቡ – የራሳቸውን ህግ እየጣሱ ሕዝብን ለመጨረስ የተነሱ እነዚህ ሃይሎች አንባገነን የሚለው ቃል አይገልጻቸውም። ካምቦዲያን አንቆ ይዞ የነበረው የፖልፖት ካመር ሩዥ እንኳን እነዚህ የሚያደርጉትን አላደረገም። ቺሊን እና ሕዝቧን የገደለው አውግስቶ ፒኖሼም አይደርስባቸውም። የመካከለኛው አፍሪካ ቦካሳ እና ከኢድያሚን ዳዳ የሚለዩት እነዚህ እስካሁን የሰው ስጋ መብላት አለመጀመራቸው ብቻ ነው።

ሕዝብ ለውጥ ይፈልጋል። ይህንን የጋለ ፍላጎት ለውጥ እንጂ ሌላ ሃይል አይመልሰውም! 25 ዓመት በአንድ የዘረኛ ፖሊሲ መገዛት ሰልችኦታል። ጥሩም ነገር ቢሆን ከመጠን ካለፈ መጥፎ ነው። ይሉናል ከበደ ሚካኤል።

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule