• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሥራ ባልደረባዬ ሆይ! እንካ ስሙኒህን!!

December 27, 2019 05:27 am by Editor Leave a Comment

አንድ አሜሪካዊ የሥራ ባልደረባዬ ተሁለት ሳምንታት በፊት አለወትሮው ቆጣ ብሎ ጸጉሩን እየነጨ ሲትከነከን አገኘሁት። “ምነው በመላጣህ ምክንያት የቁንጅና ውድድር ወደክ ወይስ የቀጠርካት ጉብል ቀረቺብህ!” ብዬ ልቀልድ ብሞክርም አለወትሮው ከንፈሮቹ አልሳሳ ጥርሶችም አልታይ አሉ። ሁለቴ ጠበቅ አድርጎ “እፍፉ…” ብሎ ታምቆ የቆዬ እስተንፋስ ከተነፈሰ በኋላ “ይህ ትራንፕ እሚባል ሰው ተቀናቃኙን ለማጥቃት ስልጣኑን መጠቀሙ ቅደመ አያቶቻችን የመሰረቱትን የአሜሪካ መሰረት የሚንድ ነው!” አለና ብሶቱን ደጋግሞ ገለጠ።  

አቶ ትራንፕ ተቀናቃኛቸውን በፖለቲካ ለማጥቃት የስልክ ንግግር ማድረጋቸው ይኸንን ጓደኛዬን እንደ ሽንኩርት ቁሊት ማትከንከኑ ገርሞኝ አይኔን አፍጥጬ ሳለሁ አንድ አገራችን እሰማው የነበረ ተረት ቁልጭ ብሎ ተፊቴ ተደቀነብኝ። “ማን? መቼ? የት? ” እያላችሁ ነፍሰ-ገዳይ ገዥዎቻችሁን ጠይቃችሁ በማታውቁት ጥያቄዎች እንደ ንፍፊት አትወጥሩኝ። ተረት ነው እማወራው ብያለሁ።

አንድ ሰው መቶ ብር ይጠፋበታል። ይህ ያልታደለ ሰው በጠፋበት ገንዘብ ልቡ እንደ እባጭ ቆስሎና አንጀቱ እንደ ሰንበር ተመትሮ ወገቡን በግራ እጁ ደግፎና በቀኝ እጁ የሚንዠቀዠቀውን እንባውን እየጠረገ እናቱ የሞተችበትን ያህል ያለቅሳል። “መቶ ብር ይኸንን ያህል ያስለቅሳል?” በሚል ከንፈራችሁን እንደ እማማ የሻረግ አሸራማችሁ አታሽሟጡ። በተረቱ ጊዜ የነበረው መቶ ብር የዛሬው ግማሽ ቢሊዮን ብር ነበር። ይህ ሰው አንዴ ጎንበስ ሌላ ጊዜ ቀና እያለ፣ በእጁ አንዴ ወደ ፊት አየሩን እየገፋ፤ ሌላ ጊዜም ማጅራቱን ጠፍንጎ እየያዘ ሰፈር መንደሩ ድብልቅልቅ እስከሚል ድረስ “ኡኡኡ!” እያለ ወዮታውን ያቀልጠዋል። 

መቶ ብር የጠፋበት ሰው ኡኡታውን በሚለቅበት ሰዓት ተዚያው ሰፈር ሌላ ያልታደለ ሰው “ወይኔ ገንዘቤ! ወይኔ ንብረቴ፣ ወይ…ወይኔ!!” እያለ እንዲያውም ከመጀመሪያው ሰውዬ ይበልጥ እንደ ክረምት ዝናብ እንባውን እያዘነበ፣ ፊቱን እየነጨ አገሩን በለቅሶ ማናጋት ይጀምራል። ነጋዴ እሚበሳጨው እራሱ ስለከሰረ ሳይሆን ሌላው ስላተረፈ ነው ይባላል። ይህንን የተመለከተ መቶ ብር የጠፋበት ሰውየም “ለካስ ተእኔም የባሰ በዚች ምድር አለ!” ብሎ በመጽናናት ለቅሶውን ገታ አደረገና ወደዚህ ወደ ሁለተኛው ሰውዬ ጠጋ ብሎ “የኔ ወንድም እንዲያው ምን ያህል ገንዘብ ቢጠፋብህ ይሆን ይህንን ያህል ፊትህን የምትነጨው?” ብሎ የሚመልሰውን ለመስማት ጆሮውን እንደ ሙሰኛ ኪስ ቦርግዶ ይጠይቀዋል። ሁለተኛው ሰውየም አጽናኝ በማግኘቱ ልቡ ረጋ ብሎ ነገር ግን ሳግ እየተናነቀው “ እንደ ወርቅም… እንደ … አልማዝም የሚ..ያበራ የሰው እጅ ያልነካው ስሙኒ” ብሎ ይመልሳል። መቶ ብር ያጣው ሰውየም ቆጣ ብሎ “የኔ ወንድም እንካ ስሙኒህን! ለቅሶዬን አታበላሽብኝ!” ብሎ ሃያ አምስት ሳንቲሙን ለሁለተኛው አልቃሽ ሰጥቶ ዝም ካሰኘ በኋላ ትቶት የቆየውን ለቅሶውን እንደገና ማቅለጥ ጀመረ ይባላል።

የሥራ ባልደረባዬ በአቶ ትራንፕ ይትከነከን የነበረው የሚሊዮኖችን ነፍስ በመደዳ እንደ ትንኝ ያጠፉ፤ እግር እንደ ግንድ የቆረጡ፤ ጥፍር እንደ ስንጥር የነቀሉና ቆዳ እንደ ሌጦ የገሸለጡ አረመኔዎች ኢትዮጵያ ውስጥ በድሎት ስልጣን ተንፈላሰው በሚገኙበት ሰዓት ነው።

የሥራ ባልደረባዬ በአቶ ትራንፕ ስልክ ጥሪ ይትከነከን የነበረው በእኛዋ አገር ተላይ በተገልጡት ወንጀሎች ተሳታፊና ተባባሪ የነበሩት ጭራቆች “ተሰማይ የወረዱ ሙሴዎች!” እየተባሉ በሚመለኩበትና በሚሸለሙበት ሰዓት ነው።

የሥራ ባልደረባዬ ተራ ወንጀልም ባልተገኘባቸው የሕዝብ ተመራጭ ይትከነክን የነበረው የእርሱ አገር አስራ አምስት እጥፍ የእድሜ ታላቅ በሆነችዋ የእኛዋ አገር መንጋዎች በዘር ማጥፋት ወንጀል በቀጥታና በተዘዋዋሪ የተሳተፉትን የሂትለር ደቀመዛሙርት እንደገና እንደ ቅርቀብ ሊጫኑ ድብዳባቸውን ተጀርባቸው እያስቀመጡ ባለበት ጊዜ ነው። መስማት ላልታከተው ዝርዝሩ ብዙ ነው።፡

ስሙኒ የጠፋብህ የሥራ ባልደረባዬ ሆይ! ጩኸትህ የእኛን በርካታ ሚሊዮን ሕዝብ ያጣነውን ጩኸት እያበላሸው ነው። እንካ ስሙኒህን! ልቅሷችንን አታበላሽብን!

4/2/2012 በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule