• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹ ‘ሮሮና ስጋት

April 18, 2014 04:08 am by Editor 2 Comments

የትምህርት ሚኒስትር በ2006 ዓ.ም በአገሪቱ በተፈጠረው የመምህራን እጥረት ምክንያት በተለ ያዩ የትምህርት ዘርፎች የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ያገኙ ኢትዮጵያውያንን ለአንድ አመት ሙሉ ወጫቸውን ችሎ የማስተማር ስነ ዘዴ (ፔዳጎጅ) በማስተማር ወደ መምህርነት እንዲገቡ ማስታ ወቂያ ያወጣል፡፡ በወጣው ማስታወቂያ መሰረ ትም ለማጣሪያነት የቀረበውን ፈተና በመፈተን መልምሎ ለስልጠና እንዲገቡ ይደረጋል፡፡ በዚህ መሰረት በ10 ዩኒቨርሲቲዎች (መቀሌ፣ ባህር ዳር፣ ወሎ፣ ወለጋ፣ ጅማ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ዲላ፣ ሀሮማያ፣ ሀዋሳና አዲስ አበባ) እንዲሰለጥኑ ይደረጋል፡፡

ይህ ስልጠና እየተካሄደ ባለበት ወቅት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ሙሉ ወጫቸ ውን መንግስት እንደሚችል ተነግሯቸው ነበር የመጡት፡፡ በዩኒቨርሲቲው መጀመሪያ የተደለ ደሉት 330 ነበሩ፡፡ ሆኖም ግን ተማሪዎቹ ቃል በተገባላቸው መሰረት መቀጠል አለመቻላቸውን ነው በቅሬታ የሚናገሩት፡፡ ወደ ዝግጅት ክፍላችን በአካል መጥተው ስለሁኔታው ያስረዱት ተማሪዎች ሁኔታውን እንደሚከተለው ያስረዳሉ፡፡ ‹‹ማስታወቂያውን አይተን ስራችን ለቀን ነው የመጣነው፡፡ ሆኖም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ሚኒስትር ቃል በገባው መሰረት ከህዳር 23 ጀምሮ የምግብም ሆነ የቤት አገልግሎት ሊሰጠን አልቻለም፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመኝታ አገልግሎት የለም በመባሉ ደብረዘይት በሚገኘው የዩኒቨርሲቲው ቅርንጫፍ የእንሰሳት ህክምና እና የግብርና ኮሌጅ ለሁለት ሳምንት እንድንቆይ ተደረገ፡፡ ሆኖም ደብረ ዘይት በሚገኘው ኮሌጅ ጥቁር ሰሌዳን ጨምሮ ለመማር ማስተማር የሚያገለግሉ አቅርቦቶች ልናገኝ አልቻልንም፡፡››

ከዚህም ባሻገር በዚህ ወቅት ተማሪዎቹ የመብት ጥያቄ እንዲያነሱ ያደረጋቸው ሌላ ምክንያትም ተፈጠረ፡፡ ‹‹ትምህርቱ በተባለው መልኩ ሊሰጠን አልቻለም፡፡ አንድ መምህር ወደ ደብረዘይት ሄዶ የሳምንቱን የትምህርት ፕሮግራም ከጠዋቱ 2 ሰዓት እስከ 6 ሰዓት እንዲሁም ከ7 ሰዓት ተኩል እስከ 11 ሰዓት ተኩል አስተምሮ ይሄዳል፡፡ ይህን ተከትሎም አንዳንድ የመብት ጥያቄዎችን ማንሳት ጀመርን፡፡›› ይላል አስተባባሪውና የጅኦግራፊ ተማሪው ጋሻነህ ላቀ፡፡

ተማሪዎቹ ሌላ ስራ ስለሌላቸውና ከቤተሰብ ውጭ ስለሚኖሩ አንዳንድ መሰረታዊ አቅርቦቶች እንዲሰጧቸው ለትምህርት ሚኒስትር ያሳውቃሉ፡ ፡ አያይዘውም የትምህርት እድል እንዲያገኙና በደሞዝ ጉዳይም ድምጽ አሰባስበው ያስገባሉ፡፡ ትምህርት ሚኒስትርም ‹‹እናንተ የወጭ መጋራት ስላልሞላችሁ የጠየቃችሁት አቅርቦት አይሰጣችሁም፡፡›› ይላቸዋል፡፡

በዚህ ሁኔታ በሁለት ሳምንት ውስጥ ወደ አዲስ አበባ ይመለሳሉ የተባሉት ተማሪዎች ለሁለት ወር ከሁለት ሳምንት በላይ (ከህዳር 24- የካቲት 8) በደብረዘይት እንዲቆዩ ይደረጋል፡፡ ከደብረ ዘይት ሲመለሱ ይዘጋጃል ተብሎ የነበረው አልጋም ሆነ ሌላ አቅርቦት አልተዘጋጀም፡፡ ይልቁንም ያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ውስጥ ከሚገኝ ባዶ ክፍል ውስጥ መሬት ላይ አራት አራት ፍራሽ እያነጠፉ እንዲተኙ ይደረጋሉ፡፡ ትምህርቱን ጥለው እንዳይሄዱ እስካሁን ያሳለፉትን ችግር ትተው መሄድ አልፈለጉም፡፡ ከዚህ ይልቅ ትምህርት ሚኒ ስትርንና አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ችግሩን እንዲፈታ በተደጋጋሚ ጥያቄ ያቀርባሉ፡፡ ይህ ጥያቄያቸው ንም እስከ ፓርላማና ሌሎች ተቋማት ድረስ አድ ርሰዋል፡፡ ሆኖም ተገቢውን ምላሽ ሊያገኙ እንዳ ልቻሉ ይገልጻሉ፡፡

በዚህ ምክንያት የተማሪዎች ችግር እንዲፈታ ጥረት የሚያደርጉ አስተባባሪዎች ጉዳዩን ወደ ሚዲያ ለማውጣት ይቆርጣሉ፡፡ የሸገር ሬድዮ ጋዜጠኞችም ጉዳዩን ተማሪዎቹ ያሉበት አካባቢ ድረስ ሄደው ይዘግቡታል፡፡ እነዚህ ተማሪዎች ከሌሎች በተለይም አስተባባሪዎቹ በሌሎች ዩኒቨ ርሲቲዎች በተመሳሳይ ሁኔታ ከሚማሩት ጋርም ግንኙነት ይመሰርታሉ፡፡ እነዚህ ተማሪዎች የሚ ያደርጉትን የመብት ጥያቄና እንቅስቃሴ አብረዋ ቸው የሚማሩ ካድሬዎች (እነሱ ሰርጎ ገቦች ይሏ ቸዋል) ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ መሆኑን ለሶስተኛ አካል (ለመንግስት) መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ከተቃዋሚ ዎች ጋርም ግንኙነት እንዳላቸው ይናገራሉ፡፡ ይህ መረጃ ለመንግስት አካላት መድረሱንም መረጃው ከደረሳቸው መካከል ውስጥ አዋቂዎች መልሰው ለአስተባባሪዎቹ ይነግሯቸዋል፡፡ አስተባባሪዎቹ የሚያነሷቸው የመብት ጥያቄዎችም ወደ አመጽ ሊቀይሩት እንደሆነ በመግለጽ መታሰር እንዳለባ ቸው መወሰኑን ይገልጻሉ፡፡ ይህንን ተከትሎም እስ ራትና አፈና ሊደርስባቸው እንደሚችል ስጋታቸውን ይገልጻሉ፡፡

አስተባባሪዎቹ ‹‹ፖለቲካዊ ጥያቄ መጠየቅ መብ ታችን መሆኑን አላጣነውም፤ ነገር ግን የአሁኑ ጥያ ቄያችን የመብት እንጂ ፖለቲካዊ ጥያቄ አይደለም›› ይላሉ፤ አክለውም ሊታሰሩ እንደሚችሉ የውስጥ ምንጫቸው በእርግጠኝነት እንደነገራቸው ይገል ጻሉ፡፡

ወጭ መጋራት በስምምነታቸው ላይ ያልነበረ ቢሆንም አሁን ግን እንደገና መጥቷል፡፡ መምህር ከሆናችሁ በአገልግሎት ዘመን፣ ሌላ ስራ ከሰራ ችሁ በገንዘብ ትከፍላላችሁ ተብለዋል፡፡ ይህ ግን ስምምነቱ ላይ አልነበረም እንደተማሪዎቹ ገለጻ፡፡ ‹‹እንዲያው ይህን ስምምነት እንሙላ ከተባለ እንኳን የሚሰጡን አገልግሎቶች ሊሟሉልን ይገባ ነበር፡፡ አሁንም ያቀረብነው አገልግሎቶች እንዲሟ ሉልን የሚል ነው፡፡ ያቀረብናቸው ቅድመ ሁኔታ ዎች ከተሟሉ ወጭ መጋራቱን ልንፈርም እንችላ ለን፡፡ እነሱ ግን በሚገባ ጥያቄያችን ሊመልሱልን አልቻሉም፡፡ እንዲያውም ምግብና ሌሎች አቅርቦቶች እንደማይሰጠን፣ ትዕዛዙ ከትምህርት ሚኒስትር የመጣ በመሆኑ ካልፈረሙ ዩኒቨርሲቲውን ለቀን ልንሄድ እንደሚገባ ሁሉ አስፈራርተውናል፡፡›› የሚለው ደግሞ የስፖርት ሳይንስ ተማሪና እንቅስቃሴውን ሲመራ የቆየው ሚሊዮን ታደሰ ነው፡፡

በተመሳሳይ ጅማ ዩኒቨርሲቲ የሚገኙት ተማሪዎች መብታቸውን ስለጠየቁ ሁለት ቀን ምግብ ከልክለው ጾም እንዳዋሉዋቸው ይገልጻሉ፡፡ በፖሊስ እያስደበደቡም ከግቢ አስወጥተዋቸዋል፡ ፡ ‹‹ባልተዘጋጀንበት ሁኔታ ትምህርቱን ጥለን አንሄ ድም!› ብለው መኖሪያቸው ቁጭ ቢሉም በፖሊስ ተከበው በመደብደባቸው በግድ የወጭ መጋራቱን ለመሙላት ተገደዋል፡፡ ከጅማ ውጭ በሌሎች ዩኒ ቨርሲቲዎች የሚገኙት ተማሪዎች የወጭ መጋራት አልሞሉም፡፡ በሶስቱ ዪኒቨርሲቲዎች (መቀሌ፣ ባህር ዳርና ወላይታ ሶዶ) የወጭ መጋራት አልተጠ የቀም፡፡ እነሱም ግን መጠየቃቸው የማይቀር ነው፡፡ ጅማ በግድ ሞልተዋል፡፡ ሌሎቹ ጋር በግዳጅ እንዲሞላ ጫና እየተደረገ በመሆኑ ያልተጠየቁትንም እንዲሞሉ ያስገድዷቸዋል፡፡››

ለተማሪዎቹ የተሰጠው ምላሽ በዚህ አያበቃም፡ ፡ ‹‹መብት ብላችሁ መጠየቅ የለባችሁም፡፡ አርፋችሁ ተማሩ›› ተብለናል፡፡ የወጭ መጋራቱን እንድንሞላ ለማስገደድ ከትምህርት ሚኒስትር ሳይቀር ሰዎች እንደተላከባቸውን ይገልጻሉ፡፡

አስተባባሪዎቹ ተማሪዎችን በማስተባበር የምንመደበው መሰረታዊ ወጭዎችን አሟልተን የማንኖርበት መምህር ነት፤ መንግስት እያዋረደው፣ ህዝብም እየናቀው ባለ ሙያ ውስጥ ልንገባ ተጨማሪ እዳ አንገባም ይላሉ፡፡ ተማሪዎቹ እንደሚሉት መንግስት አስተባባሪዎቹን በማሰር ጉዳዩን አድበስብሶ ለማለፍ ጥረት እያደረገ ነው፡፡ ‹‹በእኛ በኩል ምላሽ ካልተሰጠን ትምህርት ማቆምና ሰላማዊ ሰልፍ የማ ድረግ እርምጃዎችን እንወስዳለን፡፡ ምግብ ሊከለክሉን አይችሉም፤ ይህ በእኛ እና በአባቶቻችን ስም ተለምኖ የመጣ ነው›› በማለት መብታቸውን አሳልፈው እንደማይ ሰጡም ይናገራሉ፡፡ የዝግጅት ክፍላችን ድረስ መጥተው ስለጉዳዩ መረጃ የሰጡት የእንቅስቃሴው መሪዎች የሚከ ፈለውን መስዕዋትነት ከፍለው መብታቸውን እንደሚያስ ከብሩ ገልጸውልናል፡፡ (ምንጭ: ነገረ ኢትዮጵያ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. umer eshetie says

    April 19, 2014 07:40 am at 7:40 am

    ende mnew be zendrow amet HP temedbew university kegebu behula health extention gubu teblew ebi yalu temariwech mebarerachwn atawkum…? Weys ethiopia yetemare bekat…?

    Reply
  2. jarso says

    April 21, 2014 01:51 am at 1:51 am

    Woyane has no fear whether student or any one for that matter go out for demonstration, as woyane is aware that no body has the gut to confront and fight to death for the cause stood for. These guys do brag for what they are not committed . They would be dispersed by the sound of a single bullet and even the pubic is not sympathetic owing that the issue they have raised is trivial and reflecting their group interest. So they need to think deep as to how could connect their issues with that of the national problem . A problem how to weed out the woyane thugs ,once and for all, from the Ethiopian political scene. It is the only solution for most of our problems . Thus join hands with those genuine compatriots who raised arms for the down fall of the thugs to the end rather than staying behind the bar for showing your resentment and anger by way of going to the street. Would it not be better to die in action than being a life prisoner of the Barbarian Woyane.?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule