• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ኧረ እኔስ ጨነቀኝ”

November 4, 2013 09:58 pm by Editor Leave a Comment

ሰውየው ያገባት ሚስቱ ቤተሰቦቿ ሃብታሞች ነበሩ። እሱ ደግሞ መናጢ የሚባል ደሃ ነበር። አንድ ቀን የማይቀረው ሞት የሚስቱን አባት ነጠቀና ቀብር ወጡ። አስከሬን እየተከተሉ ሲያለቅሱ ባል ሚስቱ ጎን ሆኖ ልክ እንደሷ “አባቴ አባቴ” በማለት ያለቅስ ጀመር። ሚስትም ” የት የወለደህን ነው አባቴ የምትለው” በማለት አፍታ ወስዳ ባሏን ገሰጸችው።

ባል ለቅሶውን ቀየረና “አባቷ፣ አባቷ …” በማለት ያስነካው ጀመር። ይህን ጊዜ ሚስት አሁንም ለቅሶዋን ቆም አድርጋ “የበላኸው ጨማ፣ የጠጣኸው ጠጅ አያንቅህም? አባቷ አባቷ የምትለው” አለችው። ባልም ደንግጦ ላፍታ ዝም በማለት ካሰበ በኋላ “አረ እኔስ ጨነቀኝ፣ አረ እኔስ ጨነቀኝ … ” በማለት እያለቀሰ የባለቤቱን አባት ሸኘ። ይህ አጠር ተደርጎ የቀረበ የቀድሞ ምሳሌ ነው።

ኢትዮጵያውያን አገራቸውን ይወዳሉ። አገራቸውን በልጅ፣ በሚስት፣ በእናት፣ በአባት፣ በቤተሰብ … እየሰየሙ አንጎራጉረዋል። ተቀኝተዋል። ተደርሰዋል። ፎክረዋል። አቅራርተዋል። በዚህች አገራቸው ጉዳይ ለሚመጣ ማናቸውም ችግር “ቀልድ የለም” በማለት ልዩነታቸውን ወደ ጎን በመተው ተፋልመዋል። ወድቀዋል። ባንዲራቸውን ከፍ አድርገው ዘምረዋል።

በአንድ ወቅት ተፈጥሯል ተብሎ ከተመሰከረልን “የባንዳነት ገድል” ውጪ፣ እኛ ኢትዮጵያዊያን ጠላት ሲመጣብን፣ ወራሪ ሃይል ሲያድምብን፣ አገራችንን ሊደፍሩ የሚቃጣቸው ሲነሱብን መተባበርና አንድ መሆን ልዩ ባህላችን ነው። የምንኮራበት ስጦታችንም ነው። ጠላትን ለመመከት በተደረገ ጥሪ በገዢዎቹ አኩርፎ “ወዲያ በሉ” የሚል ትውልድ አገራችን አላበቀለችም። ጠላትን ደቁሶና አሳፍሮ የሚመልስ ትውልድ እንጂ!!

ህወሃት እመራዋለሁ የሚለውን ህዝብና አገር ወደ ጎን በማለት ከሻዕቢያ ጋር ፍቅር ተጣብቶ በቀልን በዘራበት ወቅት፣ ኢትዮጵያን የሚወዱ ዜጎችን በጠላትነት እየፈረጀ ሲወነጅል፣ የብሔር መርዝ እየዘራ አብሮ የኖረ ህዝብ ሲያጋጭ፣ አገርን ዘርፎ ለዘራፊ አሳልፎ ሲሰጥና የኢኮኖሚ አሻጥር በመፈጸም የህዝብ ሃብት ላይ ለጠቅላይ ሲጫወት፣ “ያገባናል” በማለት ለአገራቸው የሚከራከሩትን በጠራራ ጸሐይ ሲገል፣ ሲያስርና ሲያንገላታ ቆይቶ ራሱ በፈጠረው ችግር ህጻናትን በጀት ሲያስቆላ “ዞር በል” ያለው አልነበረም። ይልቁኑም ከዳር እስከዳር በመነሳት በባድመ ጦርነት ፈንጂ ላይ በመሮጥ አገርንና ህዝብን የሚያኮራ ገድል ለመፈጸም ተችሏል።

“ጦርነትን እንሰራዋለን” የሚሉት ህወሃቶች ግራ ሲገባቸው፣ እንደ ህወሃት ተግባርና ተንኮል ሳይሆን ለአገር ቅድሚያ በመስጠት ሻዕቢያን በመደቆስ ድል ከተቀዳጁ በኋላ ዳግም ክህደት ተፈጽሞባቸው ውሉ ባልታወቀ ጦርነት ወገኖቻችን አሁን ድረስ በጦር ሜዳ እሳት ዳር ተጥደው ይገኛሉ። ይህ የሚሆነው ህወሃት ሊንደው ሌት ተቀን የሚባትትበት የቀደመው የአገር ፍቅር የትብብር መንፈስ እንጂ ሌላ ኢህአዴግ የፈጠረው ውለታ ይዟቸው አይደለም። ይህ በጎ ታሪካችን ነው። አገር ወዳድ የሆንን በሙሉ እንኮራበታለን። እንመካበታለን።

በሌላ በኩል አስደንጋጭ ታሪክ አለን። ለመልካም ነገር የመተባበር ችግር አለብን። አገርን ለመታደግና በሰለጠነ መንገድ ልዩነትን የመቻቻል ጣጣ አለብን። በልዩነት ውስጥ ተባብሮ አገርን ወደ መልካም ጎዳና የማሸጋገር ራዕይና ፈቃደኛነት የለንም። የዛሬ አርባ ዓመት አካባቢ የግራው ፍልስፍና አራማጆች ነን በሚሉ የተሰበከው “በጠላቶቻችን መቃብር ላይ …” የሚል ለአንዱ ህልውና የሌላው መጥፋት ግዴታ እንደሆነ የታመነበት አስተሳሰብ እስካሁን ግራ አጋብቶን አለ፡፡ በንጉሱም፣ በደርግም ሆነ በዘመነ ኢህአዴግ ሊታረቅ ያልቻለው ይህ በሽታችን “በሞተ ስርዓትና አገዛዝ” እንድንመራ አስገድዶናል። ይህ በሽታችን ስር ከመስደዱ የተነሳ የአገራችንን ሁኔታና አካሄድ እንደ አልቃሹ ሰውዬ “አረ እኔስ ጨነቀኝ” የሚያሰኝ ሆኗል።

እርስ በርስ የመጠላለፍና አንዱን በሌላው ላይ የማሳደም፣ ራዕይና አርቆ አሳቢነት፣ ከሁሉም በላይ ቀናነት የጎደለው የተቃውሞ ፖለቲካ መንደር ለሁሉም ወገኖች ዋስትና በሚሰጥ መልኩ አለመቃኘቱ የአገሪቱን ህልውና በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ አድርጎታል። በዚሁ ሳቢያ ህወሃት የዘራው የጥላቻ መርዝ የሚያረክስ መስመር የሚዘረጋልንና በተበዳዮችና በበዳዮች ዘንድ ክብር የሚሰጠው “ተተኪ” መሪ ማግኘት አቅቶን፤ ያሉን ተቃዋሚ ሃይሎችም “በጠላቶቻችን መቃብር ላይ …” በማለት ካልፈረሰ በስተቀር መገንባት አይቻልም በሚል ግራ የገባው ዲስኩር ሰክረው ሁለት አስርት ዓመታት “አረ እኔስ ጨነቀኝ” እያልን ለመኖር ተገደናል።

ኢህአዴግ ወላልቋል። አሁን ከብበውና አንቀው ከያዙት ችግሮች አንጻር፣ እንኳን ለማይወዱት በስሙ ለሚምሉበት ግልገሎቹና ባሮቹ ዋስትናቸው ሊሆን እንደማይችል እየተነገረ ነው። ሙስናው፣ ድህነቱ፣ ፖለቲካዊ ንቅዘቱ፣ ማርጀቱ፣ በቡድን መከፋፈሉ፣ የተሳፈረበት የግፍ ባቡር ነዳጅ መጨረሱ፣ በከፍተኛ ደረጃ መተማመን የማይችሉበት ደረጃ ለመድረሳቸው ምስክር ሆኗል። ይኸው አደገኛ ወቅት አገር ወዳዶችን እያስጨነቀ ነው። አገር በቡድንና በደቦ ይመራል በሚል ዘባተሎ ምክንያት በየቀኑ የሚሰማው የስርኣቱ የመደንበር ምልክት ህግና ህጋዊነት ማክተማቸውን የሚያረጋግጥ ሆኗል። በህወሃትም ሆነ በኢህአዴግ ደረጃ አለቃና ታዛዥ መለየት አልተቻለም። የበላይና የበታች ተቀላቅሎ አቤት ማለት ያዳገተበት ወቅት ላይ ተደርሷል። “ህግ ፈረሰ፤ መንግስት ፈረሰ” ነውና !!

አሁን ያለንበት ወቅት በለውጥ ቋፍ ላይ ነው። ከውስጥም ከውጪም ራሱ ህወሃትና ድቃይ ድርጅቶቹ ዘንድ ፍርሃቻ አይሏል። በትራፊ ዘመን ከህሊናቸው ጋር ለመታረቅ የሚመኙም አሉ። ባለቀ ወቅት አገራችን እንዳለች እንድትቀጥል እርቅን የሚሹ ኢህአዴጋዊያን ጥቂት አይደሉም። የህዋሃት ሰዎችም ቢሆኑ ከዚህ የስጋት ርእደት ውጪ እንዳልሆኑ እየተሰማ ነው። በሁሉም ደጅ “አረ እኔስ ጨነቀኝ” የሚሉ በዝተዋል። ያጣነውና የተቸገርነው ለበጎ ተግባር የሚያስተባብር ጀግና ብቻ ነው። በወዳጅም፣ በጠላትም፣ በመሃል ሰፋሪውም፣ በአብዛኛው አድፋጮችም (silent majority)፣ በህወሃት ቁንጮዎችም ሆነ ሌሎች ስማቸው ባልተጠቀሱት ዘንድ ተቀባይነት ያለህ፣ ያለሽ፣ ያላችሁ፣ የጸዳችሁ፣ ያልተነካካችሁ፣ “እንከበራለን” የሚል ጽኑ እምነት ያላችሁ “አረ እኔስ ጨነቀኝ” ለሚሉ ወገኖች ድረሱ!!

ሁሉንም ወገን ነጻ የሚያወጣ ማን ነው? ማን ናት? ለሰብዓዊነት የቆመ … እንደ ሴትየዋ እንደ ራስህ ሳይሆን እኔ እንደምልህ … ከሚል የትዕዛዝና የታቃዋሚ መንግሥትነትና አምባገነንነት የራቀ፤ ራሱን ጨምሮ ሌላውን ነጻ የሚያወጣ እምነት ለኢትዮጵያ!


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ®” አቋም ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule