• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሕዝብን አፍኖና በኃይል ረግጦ መግዛት ያብቃ!

August 1, 2016 08:13 am by Editor Leave a Comment

ባለፈው እሁድ ትንሽ ትልቅ፣ ወንድ ሴት፣ ከተሜ ገጠሬ፣ ሳይል የጎንደር ሕዝብ ከዳር እስከ ዳር በነቂስ ወጥቶ ከተማዋን ባጨናነቀ መልኩ የህወሓት አገዛዝ የፈጠረውን የሽብርና የፍርሃት አጥር ሰብሮ በመውጣት የተቃውሞ ድምጹን በሰላማዊ መንገድ አሰምቶ ወደቤቱ ተመልሷል። ምንም እንኳን አገዛዙ የተቃውሞ ሰልፉ እንዳይካሄድ ማናቸውንም እርምጃዎች ቢወስድም፣ ግፍ የበዛበት፣ የቆረጠና የተባበረን ሕዝባዊ ማዕበል የሚመክተው አንዳችም ምድራዊ ኃይል የለምና ከፍተኛ ጨዋነት በተሞላው መልክ ሕዝቡ ተቃውሞውን አሰምቷል። በዕለቱ ካስተጋባቸው መፈክሮች ውስጥ “በኦሮሚያ የሚደረገው የወገኖቻችን ግድያ ይቁም” የሚለው የጎንደር ሕዝብ ምንጊዜም በኢትዮጵያዊነትና በሀገር አንድነት ላይ ያለው የሚታወቀውን ጠንካራ አቋሙን ያሳየበትና የትግል አጋርነቱን በግልጽ ያንጸባረቀበት ነው።

ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ የሕዝብ መብቶች እንዲከበሩና የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተብዬው እንዲሰረዝ በሰላማዊ መንገድ ድምጻቸውን ላሰሙ ኦሮምኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን አገዛዙ የሰጠው ምላሽ የሕዝብን ቁጣ በኃይል ለማፈን መሞከር ነበር። በዚህም ከአራት መቶ በላይ የሰው ሕይወት ጠፍቷል። የሕዝብን ቁጣ በኃይል መደፍጠጥ እንደማይቻል አገዛዙ የተማረ አለመሆኑን ያለፉት 25 ዓመታት የግፍ አገዝዙ ቁልጭ አድርገው አሳይተውናል። እስካሁን በተለያዩ አካባቢዎች በተጠቀመበት ነጣጥሎ ማዳከምና መምታት በሚለው የማፈኛ ስልቱ በትላንትና ዕለት በምሥራቅ ሐረርጌ በአወዳይ ከተማ ውስጥ ባካሄደው ጭፍጨፋ በርካታ ዜጎችን ሲያቆስል የስድስት ወገኖቻችንን ሕይወት ማጥፋቱን የተለያዩ የዜና አውታሮች ዘግበዋል። ህወሓት በጎንደር በተካሄደው ሰላማዊ ተቃውሞና ሕዝባዊ ማዕበልን መቋቋም እንደማይችል ምናልባት ተረድቶት ይሆናል የሚለውን ግምት ውድቅ እንዳደረገው እነሆ በአወዳይ ከተማ የፈጸመው ጭፍጨፋ ፍንትው አድርጎ አሳይቶናል። በመሆኑም ይህን ህወሓት የፈጸመውን አረመኔያዊ ድርጊት የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ አጥብቆ ያወግዛል።

ጆሮ ያለህ ስማ እንዲሉ የህወሓትን አፋኝ፣ ጨፍጫፊ፣ ዘረኛና አምባገነን ቡድን ማስታወስ የምንወደው በዓለም ዙሪያ የነበሩ አምባገነን አገዛዞች ሁሉ በውርደት ከሥልጣን መወገዳቸውን ቢያንስ የመንግሥቱን፣ የሙባረክን፣ የጋዳፊን፣ የሳዳምን…ወ.ዘ.ተ እጣ ፈንታ እንዴት እንደነበረ ነው። ስለዚህ የሥልጣን ምንጭና ባለቤት የሆነውን ሕዝብ መብት
አፍኖና በኃይል ረግጦ ለዘለዓለም መግዛት እንደማይቻል ተረድቶ ሕዝብ ለእልቂት፣ ሀገርም ለበለጠ ጉዳት ከመዳረጓ በፊት መብቱን በሰላም ለጠየቀ ሕዝብ ትክክለኛው ምላሽ እንዲሰጠው ይገባል እንላለን። ይህ ሳይሆን ቢቀርና ህወሓት እስካሁን በተከተለው ጎዳና ከቀጠለ ለሚደርሰው የሕይወት መጥፋትና የንብረት መውደም ተጠያቂው ህወሓት ብቻ
መሆኑን ከወዲሁ መግለጽ እንወዳለን። ሕዝቡ የሀገር አንድነቱን ጠብቆ መብቱን በሰላማዊ መንገድ ለማስከበር የሚያደርገውን ትግል የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ እንደሚደግፍ በማያሻማ ቋንቋ እየገለጸ፣ በሚችለው ሁሉ ለመተባበር ዝግጁ መሆኑን ያረጋግጣል።

አንድነቷ የተጠበቀ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ በሕዝብ ትግል ትመሠረታለች!

ሐምሌ 26 ቀን 2008 ዓ. ም (August 2, 2016)

Tel: 44 7937600756 , +1 9168486790 E-mail : shengo.derbiaber@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule