• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሰላም ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ፋንታሁን ብርሃኑ ታሰረ

November 7, 2014 08:12 pm by Editor 1 Comment

ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በማስተባበርና በማቀራረብ እርቅ ለማስፈን እንደሚንቀሳቀስ የሚነገርለት የመግባባት፣ አንድነትና ሰላም (ሰላም) ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ፋንታሁን ብርሃኑ መታሰሩን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ አቶ ፋንታሁን የታሰረው ‹‹የሰላም ጥሪ›› በሚል ነጭ ሰንደቅ አላማ በማውረብለብና የማህበሩን አላማ የሚገልጹ፣ እንዲሁም ማህበሩ በአሁኑ ወቅት ለአገሪቱ ችግር የሚላቸውን ጉዳዮች በዝርዝር የያዘ በራሪ ወረቀት ለህዝብ በመበተን ማህበሩን በማስተዋወቅ ላይ በነበረበት ጊዜ እንደሆነ ታውቋል፡፡

በራሪ ወረቀቱ የህሊና እስረኞች መፈታት እንዳለባቸው፣ መንግስት በሀይማኖቶች ላይ ጣልቃ መግባት እንደሌለበት፣ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ዜጎችን ማፈናቀሉ እንዲቆምና መንግስት በተቋማት ላይ ከሚያደርገው ጣልቃ ገብነት እንዲቆጠብ የሚመክሩ ሀሳቦች እንዳሉበት ለማወቅ ተችሏል፡፡

ነጭ ሰንደቅ አላማ ሲያውረበልብ፣ የማህበሩን አላማና በህዝብ ላይ አሉ ያላቸውን ችግሮች ለህዝብ ሲያስተዋወቅ የተያዘው አቶ ፋንታሁን ህዝብን ለማነሳሳትና አመጽ ለመቀስቀስ ሙከራ በማድረግ በሚል እንደተከሰሰም ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

አቶ ፋንታሁን እሁድ ጥቅምት 23 ሽሮ ሜዳ አካባቢ በራሪ ወረቀት ሲበትን ተይዞ ላዛሪስት በሚባለው ፖሊስ ጣቢያ ታስ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡ (ምንጭ እና ፎቶ: ነገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    November 7, 2014 11:10 pm at 11:10 pm

    አቶ ፋንታሁን ህዝብን ለማነሳሳትና አመጽ ለመቀስቀስ ሙከራ በማድረግ በሚል ተከሰሰ:
    “ነጭ ሰንደቅ አላማ ሲያውረበልብ፣ ለሕዝብ በሰጠው በራሪ ወረቀቱ ላይ፡_
    * የህሊና እስረኞች መፈታት እንዳለባቸው፣!
    *መንግስት በሀይማኖቶች ላይ ጣልቃ መግባት እንደሌለበት፣!
    * በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ዜጎችን ማፈናቀሉ እንዲቆም!
    *መንግስት በተቋማት ላይ ከሚያደርገው ጣልቃ ገብነት እንዲቆጠብ!
    የሚመክሩ ሀሳቦችንና የማህበሩን አላማና ለህዝብ ሲያስተዋወቅ ነው።አራት ነጥብ።
    *******************!
    ***መንግስት ያሠረው በበራሪ ወረቀቱ ላይ ያለውን ፈፅሜአለሁ ምንአገባህ ብሎ ነው?
    ***በሕገመንግስቱ ይህ ለገዢው ፓርቲ ብቻ ይፈቀዳል ብሎ ነው?
    ***ይህንን ድርጊቴን ህዝብ የመቀበል ግዴታ አለበት ብሎ ነውን?
    ***ሕዝቡ እየተሰደበ እየተረገጠ በትናንሽ ጥቅማጥቅም ተይዞ ይኖራልና ችግሩን አትንገረው ብሎ ይሆን?
    ***ይህ ሌላ አማራጭ የሌለው ሕዝብ በሙሉ ፍቃደኛነት ሊረገጥ ተስማምቷል ብሎ ነው?
    *** ለእኛ በእኛ ሰው የሆነ ያለእኛ ምንም የማይሆን ግን ተበታትኖ የሚጠፋ ነው ብሎ ተማምኖ ይሆን?
    *** በፈጣንና አሳላጭ መንገድ በቅፅበት የሚያድገው ከሕዝብ በላይ ከመንግስት በታች የሆነው ቡድን ይሆን?
    ***የነጭ ባነዲራ ትርጓሜ ያልገባቸው ብጥብጥ ወዳድ(እነጭር ሲል አንወድም ይሆኑ?)
    *** ይህ ጭፍን ደጋፊ(ተደጋፊ)…ጭፍን ተቃዋሚ(አቋቋሚ) ዕርቅ ሰላም አንድንት ኀብረት ያቃዣቸው ይሆኑ?
    ***በእርግጥም አውራው ገዢ ፓርቲ ተራራ ውጡና፣ ገደል አቋርጡና ጉልበቴን ፈትሹ ብሎ እየገፋ ይሆን?
    *** መንቀሳቀስ፣ መዘዋወር፣ መሰለፍ፣ መሰብሰብ፣ በከልልና በክልከላ ከተለወጠ ዜግነት ቀርቶ በሊዝ መኖር ተጀመረ?
    ***በውስጥ የብሔርና ቋንቋ ብጥብጥ የቡድን መናቆር ትርፋማ የሆኑ ተደራጅተው አቆብቁበው እየጠበቁ ይሆን?
    “ማንም ሰው በፖለቲካ አመለካከቱ አልታሰረም! ሊታሰርም አይገባም!ኢህአዴግ ከስሕተቱ ይማራል! ከተባለ..የሰላም ማኅበር ማቋቋምና የህዝብ ብሶትን ለመንግስት ማሳወቅ በየትኛው ሕግና ሰንደቅ ወንጀለኛ ያደርግ ይሆን?
    _____ለመሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝባዊ መከላከያ ለሕዝብ፣ ለሀገር ሉዓላዊነት ከቆመ ይህንን የተበላሸ(የበሰበሰ) ሥርዓት መምከር ወይንም የከፋ ውጥንቅጥ ውስጥ ከመግባታችን በፊት ማንአለብኝነት፣ የህዝብ ንቀት፣አምባገነን፣ የወሮ-በላ ቡድን እንዲወገድ አስተዳደሩን በሠላም ተረክቦ ለፍትሀዊ አስተዳዳር ማስረከብ ሀገራዊ ቃለ-መሐላ ግዴታ የገባበት፣ ኀላፊነትም የወሰደበት ለግለሰብና ለፖለቲካ ፓርቲ ዕድገት፣ ብልፅግና ሳይሆን ለሕዝብ ሠላምና ደህንነት መሆኑን አይዘንጋ!። ሠላም ለሁሉም።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule