• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የብሔራዊ እርቅና መግባባት ጉዳይ

August 23, 2014 03:17 am by Editor Leave a Comment

ስለ ብሔራዊ እርቅና መግባባት ጉዳይ አጠር ምጥን ተደርጎ የተዘጋጀውን ባለ አምስት ነጥብ የዳሰሳ ጥናት (survey) ለዚሁ ጉዳይ ሲባል ብቻ ወደ ተዘጋጀው ድህረገፅ እዚህ ላይ በመጫን  በመሄድ ድምፅዎን ያሰሙ።  የዝምተኛው ብዙሃን ድምፅ ጭምር ሳይቀር እስቲ ይሰማ!

ፖለቲካውንና ፍልስፍናውን አርባ አመት አውጠንጥነን አረጀንበት። እንዲሁ ስንባዝን እድሜያችን አልቆ አንድ ባንድ ወደ ሞት ልንሄድ ነው። እርቅና መግባባትን ማን ጠላ? መላው ጠፍቶብን እንጂ። አይ መላውም አልጠፋን እንደ እውነቱ ከሆነ። ኢትዮጵያ መፍትሔ ሊያመጡ የማይሳናቸውን ልጆች ወልዳ ሳለ እንደ መካን ቁጭ ብላ መቆዘም አይገባትም። እስቲ የልበ ሰፊው፦ የአስተዋዩና የጨዋው ሕዝብ ድምፅ እንስማው።

ባለስልጣኑ በራሱ ጡንቻ ተማምኖ ተቃዋሚውን ከመንጫጫት በላይ ምን ያመጣል ብሎ ሲንቅ፦ ተቃዋሚው ምንም ይሁን ምን ባለስልጣኑ ከመንገድ ይጥፋ ብሎ በጥላቻ ሲሞላ፦ ኢትዮጵያ በመሃከል እፎይታን ሳታይ አንዱ ትውልድ እያለቀ ሌላው ትውልድ ያንኑ የመከራ ቅርስ ሊወርስ ዛሬ ደረስን።

recon11ንቀት ውላ ስታድር ውድቀትን ትከናነባለች። ጥላቻ ጊዜዋ ደርሶ በተራዋ ስልጣን ላይ ስትወጣ ንቀትን ትላበስና ታሪክ ራሱን ይደግማል። ታዲያ ከዚህ የመኝታ ቅዥት ወደ ፈውስ የሚያመጣን እርቅና መግባባት ብቻ ሳይሆን አይቀርም።

ሁላችንም እንንቃ። የአርባ አመታት የመከራ ጉዞ እጅ እጅ ይበለን። ባለስልጣኑም ሆነ ተቃዋሚው አንዱ ያለ ሌላኛው ለኢትዮጵያ ዜሮ መሆኑ ይግባው። ሁለት ዜሮ ምን ፋይዳ ይፈጥራል? ወደ እግዚአብሔር እንጩህ፦ ትንቢተ ኤርምያስ  33፡3 እንዲህ ይለናል፦ “ወደ እኔ ጩኽ፥ እኔም እመልስልሃለሁ አንተም የማታውቀውን ታላቅና ኃይለኛ ነገርን አሳይሃለሁ።” በብሔራዊ ደረጃ የአምላክን እርዳታና በረከት መጠየቅ አይታፈርበት። ሳናሰልስ ሁላችንም “የኢትዮጵያ አምላክ ኢትዮጵያን አስባት” ብሎ መማፀን የኢትዮጵያዊነት ምልክት ይሁንልን።

እባክዎን አምስት ደቂቃ ይውሰዱና የተዘጋጀውን ባለ አምስት ነጥብ የዳሰሳ ጥናት ላይ ይሳተፉ። ኢትዮጵያዊ መቼ ተባብሮ ቁም ነገር ይሰራና ለሚሉት መልስ እንስጥ። ኢትዮጵያ ትጎበኝ ዘንድ በደጅ ነው። ገና ምኑ ገና፦ ኢትዮጵያ ሁሉም እፎይ ብሎ የፍቅር መንደር እስክትሆን ድረስ ነፍሳችን አታርፍም። ስለ ተሳትፍዎ እግዚአብሔር ያክብርልኝ። እግዚአብሔር ለሁላችንም እጅግ አስቸጋሪ የሆነብንን የኢትዮጵያ እንቆቅልሽ ይፍታ። አሜን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule