• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሮመዳን ዋዜማ እና ሮመዳን በሳውዲ

July 9, 2013 02:19 am by Editor Leave a Comment

እንኳንስ ለኔ ቢጤ አፍላ የጎልማሳነት እድሜውን በሳውዲ እየገፋ ላለ ላንድ ሰሞን ጉብኝት ሳውዲን የመጎብኘት እድልን ላገኘ የሮመዳን ወር የጾምና የጸሎት ወር ልዩና የማይረሳ ትዝታ ይቋጠርበታል፡፡ በሮመዳን ዋዜማ የገበያ ጥድፊያramadan 1 የተለመደ ነው፡፡ ጾሙን ለመያዝ የሚያስችሉ የምግብ ፍጆታና ቁሳቁሶችን ዋዜማ መገለጫ ሆኖ ከአመት አመት የሚስተናገድ ቀልብን ሳቢ ትዕይንት ነውና በዛሬው የማለዳ ወጋወጌ ስለ ሮመዳን ዋዜማ ከማውቀው ጥቂቱን ላካፍላችሁ ወድጃለሁ ! የፈቀዳችሁ ተከተሉኝ. . .

. . . ጾም ሲፈታ ለሚቀርበው የጾም መፍቻ ተምርና ጣፋጭ መጠጦች ጨምሮ የምግብ ማዕዱን ramadan 3ለማድመቅ ታላቅ ቅናሽን በሚያደርጉት ትላልቅ የገበያ አዳራሾች የሚደረገው ግብይት ደምቆ የሚስተዋለው በሮመዳን ዋዜማ ባሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ ነው፡፡ ለአረቦች ነዳጅ ለሰጠ ፈጣሪ ምስጋና ይግባውና የዘመኑ ቴክኖሎጂ የወለዳቸው የተለያዩ የባውዛ መብራቶችና የሌዘርramadan 2 አንጸባራቂ ብርሃኖች አውራ መንገዶችንና የህዝብ መዝናኛ ቦታወችን የማድመቁ ሃላፊነት የሳውዲ መንግስት ሃላፊነቱን ሲወጣ የሚታየው የሮመዳንን በአል ለመቀበል ሽር ጉድ የሚባልበት አጋጣሚም ይህ የዋዜማ ወቅት ነው ! በሮመዳን ጂዳ እጹብ ድንቅ የሚታይባት ሙሽራ ናት ቢባል ማጋነን አይሆንም !

በሮመዳን ሰውም ቸር ነው ! . . . በየመንገዱ ሲያልፍ ሲያገድም ሰላም ሳይባባል አይተላለፍም፡፡ በተለይ በጾሙ ወቅት ለአንድየ ሰላምታ ” አውቀዋለሁ ፣ አላውቀውም” የሚባል ነገር አይሰራም፡፡ ፈገግ ብሎ በሰላምታ ከመጨባበጥ ባለፈ አብሮ እንዳደገ ትከሻ ለትከሻ ሰላምታ መለዋወጥ የተለመደ የሮመዳን ወር ልዩ ህበረ ቀለማዊ ውበት ነው፡፡ ቀን ላይ ሁሉም ምግብ ቤቶችና ሻሂ ቤቶች ዝግ ናቸው፡፡ ከረፋዱ ጀምሮ ቢሮዋቸውን የሚከፍቱት በአብዛኛው ከውጭ ኩባንያዎች ጋር ትሥሥር ያላቸው ጽህፈት ቤቶች ፤ ለሮመዳን ፍጆታ ምግብ መጠጥ ምኑ ምናምኑን የሚያቀርቡት ፋብሪካዎችና ከዚሁ ጋር ተዛማጅ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ሱቆች ብቻ ናቸው፡፡ ቀኑ ወደ ማታ የተቀየረ ይመስላል፡፡  ጾሙ ከተፈታ በኋላ ምሽት ላይ ምግብ ሲበላ እንደ ሃገራችን ሰው በቅርቡ ያለውን ይጋብዛል “ፈደል” ይሉታል ! “እባክህ እንብላ !” እንደ ማለት ነው፡፡ እንብላ ብሎ አንዱ አንዱን ሲሸማግል ማየት የተለመደ ነው !

ጅዳ በምትደምቅበት ወቅት በሮመዳን ሁሉም ነገር የሚሆነው ማታ ነው፡፡ ታዲያ ማታ ይህ ሁሉ ሲሆን ቀን ላይ ጥድፊያ አይታይም፡፡ አውላላውን ጥርጊያ መንገድ ሞልተው የሚርመሰመሱት ሚጢጢዎችም ሆኑ ትላልቅ የቅንጦት መኪኖችም አልፎ አልፎ ውር ውር ከማለት ባለፈ ብዙ አይታዩም፡፡ ከተማዋ የተወረረች ትመስላለች፡፡ ቀን ላይ ሃይማኖቱ ምንም ይሁን ምን እንደ ሲጋራውና እንደ ምግቡ ሁሉ ውሃ መጠጣት እንኳ አይፈቀድለትም፡፡ “መምኑእ” ነው ክልክል ! በሳውዲ ! በሮመዳን ጾም ዋዜማ የሚፈልገውን ሁሉ እቤቱ ከዋውኖ መውጣት ግድ ይላል ! የስሞኑ ናላን ሰብሮ የሚገባው የጅዳን ሃሩር ጸሃይና የቀይ ባህር ወበቅ አይጣል ነው! . . .ዛሬ በዋዜማው ያለሁት ከመካ 80 ኪሌ ሜትር የቅርብ ርቀት በምትገኘው በወደብ ከተማዋ በጅዳ ነው! አምና ይህን ሰአት ድግሞ ከልጆቸ ጋር የሮመዳንን ዋዜማ የመጨረሻ ቀን የተቀበልኳት ኮረብታማ እናramadan kareem ረባዳ በሆነችው ከተማ ጣይፍ ላይ ሆኘ መካን ቁልቁል እያየኋት ነው ! . . . በቀጣይ አመታት የት እንደምሆንም ብቻ ሳይሆነ እኖር አልኑር፣ የሚያውቀው አንድየ ብቻ ነው!

በዘንድሮው ሮመዳን ቅዱሳኑ መካና መዲና እንደለመዱት ከመላ አለም ለጸሎት የሚመጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ምእመናን ሙሉ በሙሉ አይስተናገድባቸውም ። ምክንያት አለው ፣ታላቁ የካእባ እና የመዲና ቅዱሳን ቦታዎችን ለማስፋፋት ፣ ከአመት እስከ አመት ተንቦርቅቆ ውሎ የሚያድረውን የበርሃ ሃሩር ወደ ኤሌትሪክ ሃይል ለመቀየር ፣ ትላልቅ ማረፊያ ሆቴሎች ለመገንባት እና ቅዱሳኑን ቦታዎች በፈጣን ዘመናዊ ባቡር ለማገናኘት በቢሊዮኖች የሚቆጠር መዋዕለ ንዋይ ተመድቧል። ከግንባታው ጋር መጨናነቅ እንዳይፈጠር የጸሎተኞች ቁጥር እንዲቀንስ መደረጉን የሳውዲ መንግስት አስታውቋል። በዚህ መሰረት ከሃገር ውስጥ የጸሎተኞች ኮታ በ50 እጅ የቀነሰ ሲሆን የውጭ ምዕመናን ኮታ በ20 እጅ እንዲቀንስ ተደርጓል ! ግንባታው ሲጠናቀቅም የመካና መዲና የቅዱስ ቦታዎች የማስተናገድ አቅም በእጥፍ ድርብ እንደሚጨምር በዋዜማው ያሰባሰብኳቸው መረጃዎች ለሮመዳኑ ዋዜማ የማለዳ ወጌ ግብአት ሆነውኛል!

እንኳን ለሮመዳን የጾምና የጸሎት ወር በሰላም አደረሳችሁ !

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule