• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

80ኛው ዓመት የየካቲት 12 የሰማእታት ቀን ዝክረ-በዓል

March 24, 2017 05:20 am by Editor Leave a Comment

ጋዜጣዊ መግለጫ   

በ1929 ዓ/ም ፋሺሽት ኢጣልያ 30000 ኢትዮጵያውያንን በአዲስ አበባ ከተማ በሶስት ቀኖች ውስጥ የጨፈጨፈችበት 80ኛ የየካቲት 12 ቀን ዝክረ-በዓል በዓለም-አቀፍ ደረጃ ተከብሯል። እስካሁን ለድርጅታችን በደረሰው ዜና መሠረት፤ በዓሉ በአዲስ አበባ፤ በዳላስ፤ በአትላንታ፤ በማያሚ፤ በኒውዮርክ፤ በዋሺንግተን ዲ.ሲ.፤ በሮም፤ በኮሎኝ፤ በአውሮራ፤ በቫንኩቨር፤ በቶሮንቶ፤ በሲያትል፤ በፕሪቶሪያና በስቶክሆልም ተከብሯል። የአከባበሩም ዘዴ በአብዛኛው በጸሎት ሲሆን፤ እንደ ዳላስ፤ ኒውዮርክ፤ ፕሪቶሪያና ሮም ባሉ ከተሞች በጉባኤ፤ እንዲሁም በዋሺንግተን ዲ.ሲ. በሰላማዊ ሰልፍ ተከናውኗል።

ካጋጠሙት እጅግ የሚያበረታቱ ክስተቶች ውስጥ፤ ከፍ ያለ ምሥጋና የሚገባቸው የመገናኛ ብዙኃን ስለ ሰማእታቱ ቀን ሰፊ ግንዛቤ እንዲገኝ ያበረከቱት አስተዋጽኦ ነው። እነዚህም ቪ.ኦ.ኤ. ሬዲዮ፤ የጀርመን ሬዲዮ፤ ኢሳት፤ ሕበር ሬዲዮ፤ ኢ.ቢ.ኤስ (ርእዮት)፤ የዳላስ ኢትዮጵያ መረዳጃ ማሕበር ሬዲዮ፤ ማሕደረ ሬዲዮ፤ ጣና ሪዲዮ፤ እና ኤስ.ቢ.ኤስ (አውስትሬሊያ) ሬዲዮ ናቸው።

ከተገኙው መልካም ውጤቶች ውስጥ፤

(ሀ) ቫቲካን፤ ፋሺሽት ኢጣልያን ደግፋ ስለ ነበር፤ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ ከታች በተመለከተው ድረ-ገጻችን የሚገኘው አቤቱታ በ700 ተጨማሪ ሰዎች በላይ ተፈርሟል። ባሁኑ ጊዜ የፈራሚዎች ቁጥር 5600 ቢደርስም የሚፈለገው 100000 ስለሆነ ተጨማሪ ጥረት እንደሚያስፈልግ ግልጽ ነው።

ፎቶ: ከግራ ወደቀኝ አቶ ጣሰው መልዓከህይወት፣ አቶ ከባዱ በላቸው እና ጠበቃ ፍጹም አቻምየለህ አለሙ

(ለ) በኢጣልያ፤ ሮም ከተማ በተከናወነው፤ በአብዛኛው ኢጣልያኖችና ጥቂት ኢትዮጵያውያን በተገኙበት ጉባኤ፤ ውይይቱ ያተኮረው በኢትዮጵያ ላይ ተፈጽሞ ለነበረው የጦር ወንጀል ተጠያቂ የነበሩ ፋሺሽቶች የጀርመን ተጠያቂዎች ነረምበርግ  (Nuremburg) በተሰኘው የፍትሕ ሥርዓት እንደ ተከሰሱ ወንጀል ፈጻሚ የነበሩ ኢጣልያኖችም ለፍትሕ መቅረብ እንደነበረባቸው ሐሳቦች በመለዋወጥ ነበር።

(ሐ) ሮም በተከናወነው ጉባኤ የተነሳው ሌላው አርእስት “የኢትዮጵያ ጨፍጫፊ” በመባል ለሚታወቀው ለሮዶልፎ ግራዚያኒ፤ የቫቲካን ተወካይ በተገኙበት፤ እ.አ.አ. በነሐሴ 2012 ስለ ተመረቀለት መታሰቢያና መናፈሻ ነበር። አፊሌ በምትባል የኢጣልያ ከተማ የሚገኘው መታሰቢያ እንዲወገድና ለጉዳዩም ተጠያቂ የሆኑት የከተማው ከንቲባ እና ምክትል ከንቲባ የእስር ፍርድ ተበይኖባቸው ጉዳዩ በይግባኝ በመታየት ላይ ቢሆንም ሮም የሚገኙ የኢትዮጵያ ወዳጆች በቅርብ እየተከታተሉት ነው።

ፋሺሽት ኢጣልያ በኢትዮጵያ ላይ ለፈጸመችው እጅግ ከባድ የጦር ወንጀል፤ አንድ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን በመጨፍጨፋቸው፤ 2000 ቤተ ክርስቲያኖች፤ 525000 ቤቶችና 14 ሚሊዮን እንስሶች በመውደማቸውና ብዙ ንብረት በመዘረፉ እንዲሁም ቫቲካን ለፋሺሽቶቹ ስለ ፈጸመችው ድጋፍ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይቅርታ እንዲጠየቅና ተገቢው ካሣ እንዲከፈለው፤ ድርጅታችን ጥረቱን እየቀጠለ ነው፡፡

ቸሩ የኢትዮጵያ አምላክ ለውድ ሐገራችን የሚገባውን ፍትሕ እንድናስገኝ ይርዳን።

ዓለምአቀፍሕብረትለፍትሕ – የኢትዮጵያጉዳይ

4002 Blacksmith Drive, Garland, TX 75044; Tel: (214)703 9022

www.globalallianceforethiopia.org; E-mail: info@globalallianceforethiopia.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule