• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤ/ክ ጠቅላላ መንፈሳዊ ጉባኤ የአቋም መግለጫ

May 21, 2013 10:24 pm by Editor Leave a Comment

የርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላላ መንፈሳዊ ጉባኤ የአቋም መግለጫ

ግንቦት ፲፩/ ፪ሺ፭ (19th May 2013)

የርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላላ መንፈሳዊ ጉባኤ፤ ከእዚህ በፊት የቤተ ክርስቲያኗን አስተዳደር አቋም፣ የውስጥ መተዳደሪያ ደንብና ትረስት ዲድ በሚመለከት ያሳለፋቸው ውሳኔዎችና መግለጫዎች ሙሉ በሙሉ እንደተጠበቁ ሆነው፤ የቤተ ክርስቲያናችንን ችግር ለመፍታት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የተከሰቱ፣ የተሳሳቱ መረጃዎችንና መግለጫዎችን ለማስተካከል፤ ጠቅላላ መንፈሳዊ ጉባኤው የሚከተለውን የአቋም መግለጫና ማብራሪያ አውጥቷል።

1)  የርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ግንኙነቷ አዲስ አበባ ከሚገኘው ቅዱስ ሲኖዶስ ሲሆን፤ አስተዳደሯ ግን በቃለ ዓዋዲው፣ በ2006 ባወጣችው ደንብ፣ በተሻሻለው ትረስት ዲድና በእንግሊዝ ቻሪቲ ሕግ መሰረት (አስተዳዳሪን ጨምሮ) በምትመርጣቸው የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ አባላት ወይም ባላደራዎችና ልዩ ልዩ ንኡንስ ኮሚቴዎች አማካኝነት/መሰረት ብቻ፤ ያለማንም የውጪ አካል ጣልቃ ገብነት ራሷን ችላ ትተዳደራለች። የቤተ ክርስተያኗም ንብረት አስተማማኝ በሆነ መንገድ ለመጪው ትውልድ ለማቆየት በሚያስችል መንገድ፤ የቤተ ክርስቲያኗ አባላት ብቻ በሚያጸድቁት ደንብ/ሕግ መሰረት ይያዛል፣ ይጠበቃል።

2)  የርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የአስተዳደር መሰረቶች፤ በ2006 ዓ.ም. የጸደቀው፤ የውስጥ መተዳደሪያ ደንብ፣ ትረስት ዲድና ከእዚህ በፊት የጠቅላላ መንፈሳዊ ጉባኤው ያወጣቸው የአቋም መግለጫዎችና በእዚህ ሰነድ በተራ ቁጥር አራት ላይ በተጠቀሰው መሠረት ተሻሽለው፤ በጠቅላላ መንፈሳዊ ጉባኤው የሚጸድቁ የውስጥ መተዳደሪያ ደንቦች፣ የትረስት ዲድስ፣ የአቋም መግለጫዎችና ውሳኔዎች ብቻ ናቸው።

3)  የመንበረ ጵጵስና ሀገረ ሰብከትን በሚመለከት፤ ቤተ ክርስቲያኗ ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ የምትመራበትና የምትተዳደርበት የውስጥ ደንብ በሚያዘውና ቤተ ክርስቲያኗ ባወጣችው የአቋም መግላጫ መሠረት በመሆኑ፤ አሁን ተቋቁሟል በተባለው “የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት” ውስጥ፤ የርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ምንም ዓይነት ተሳትፎና ግንኙነት ስለሌላት፤ ለሀገረ ስብከቱ እውቅና አትሰጥም። ለወደፊት ከሀገረ ስብከት ጋር የሚኖራት ግንኙነት የቤተ ክርስቲያኗ አባላት ተነጋግረው የሚወስኑት ጉዳይ ነው።

4)  የቤተ ክርስቲያኗ የውስጥ መተዳደሪያ ደንብና ትረስት ዲድ፤ ጠቅላላ መንፈሳዊ ጉባኤው በ 14/04/2013 ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት፤ አሁን ባሉት አርቃቂ ኮሚቴ አስረጅነትና በተቋቋመው ገለልተኛ አወያይ ኮሚቴ መሪነትና ሊቀ መንበርነት፤ በአዲሱ የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ አስተነባባሪነት፤ ተጠናቆ ሲጸድቅ ሌላ አዲስ የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ (ባላደራዎች) ይመረጣል።

5)  አሁን በቤተ ክርስቲያናችን ውሰጥ የተከሰተው ችግር፤ የሃይማኖት/እምነት ችግር ሳይሆን የአስተዳደር ችግር ስለሆነ፤ ከላይ በተራ ቁጥር አንድ በተጠቀሰው መሠረት ለችግሩ መፍትሔ የሚሰጡት የቤተ ክርስቲያኗ አባላት ብቻ ስለሆኑ፤ ቅዱስ ሲኖዶሱም ሆነ ቤተ ክርስቲያኗ እውቅና የማትሰጠው “ሀገረ ስብከት” ችግሩን ለአባላቶች በመተው የቤተ ክርስቲያኗ አባላት በውስጥ ደንባችንና በእንግሊዝ ሀገር የቻሪቲ ሕግ መሠረት እንድንፈታው ይሆን ዘንድ በትህትና እያሳሰብን፤ ጸሎታቸውና ቡራኬአቸው ግን እንዳይለየን እንጠይቃለን።

6)  ከላይ በተጠቀሰው መሠረት የቤተ ክርስቲያናችን ችግር የሚፈታው በአባላቷ ብቻ ስለሆነ፤ የሌሎች አብያተ ክርስቲያናት አባላት (የቅድስት ሥላሴ፣ የቅዱስ ገብረኤልና የጸራጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንና የሌሎች በለንደንና አካባቢው የሚገኙ የአብያተ ክርስቲያናት አባላት) በቤተ ክርስቲያናችን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገቡብን ከታላቅ አክብሮት ጋር አበክረን እናሳስባለን። ይህ በአንድ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ውስጥ የሌላ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ጣልቃ ገብነት፤ በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ አለመግባባትና ከፍተኛ ቅራኔን የሚጭር ከመሆኑም በላይ፤ በሕገ ቤተ ክርስቲያንም ሆነ በእንግሊዝ ሀገር የቻሪቲ ሕግ ተቀባይነት የሌለው ሕገ ወጥ ተግባር እንደሆነ ለማስገንዘብ እንወዳለን።

7)  በለንደንና አካባቢዋ ያሉ ካህናት፤ ሰሞኑን ከአዲስ አበባ ለመጡ ሁለት ሊቃነ ጳጳሳት የአቋም መግለጫ በማውጣት ፈርመው መስጠታቸውን ለማወቅ ተችሏል። ይህ የካህናቱ መግለጫም ሆነ አቋም ግን የርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንን ካህናትና ምዕመናን የማይመለከትና ተቀባይነትም የሌለው መሆኑን አጥብቀን እናሳውቃለን።

8)  በተራ ቁጥር 7 ላይ የተጠቀሰውን መግለጫ፤ የተወሰኑ የለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ወይም አገልጋይ የነበሩ ካህናት ተሰማምተው መፈረማቸውን ለማወቅ የተቻለ ሲሆን፤ ይህንን ግን ጠቅላላ መንፈሳዊ ጉባኤው የማይደግፈውና የማይቀበለው ሲሆን፤ ካህናቱም ተስማምተው የፈረሙት በግል ስማቸው ብቻ እንጂ የርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያምን ካህናትና ምዕመናን ወክለው አለመሆኑን አጥብቀን እናስገነዝባለን።

9)  በቀድሞው የለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ቆሞስ አባ ግርማ ከበደና፤ በጥቂት የቀድሞው የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ አባላት አማካይነት፤ ከሌሎች ደብሮች ጋር በመተባበርም ሆነ በግል የሚወጡ የአቋም መግለጫዎችም ሆነ ምርጫዎች፤ የርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ጠቅላላ መንፈሳዊ ጉባኤ የማይደግፈውና የማይቀበለው ከመሆኑም በላይ ሕጋዊነት የሌለው መሆኑን አጥብቀን እናሳውቃለን።

10) የርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ጠቅላላ መንፈሳዊ ጉባኤ፤ በ21/04/2013 ባደረገው ስብሰባ ላይ 9 አባላት ያሉት አዲስ የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ አባላቶች/ባላደራዎች መምረጡ ይታወሳል። ይህ አዲስ የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ የስራ ሃላፊነቱን ከቀድሞው የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ መረከብ ይችል ዘንድ የተጀመረው የሕግ እንቅስቃሴ እንዲቀጥልና የቻሪቲ ኮሚሽን ባዘዘው መሰረት ተወካዮቻችን፤ በተጀመረው የሚዲዬሽን(Mediation) ስራ መሠረት ጉዳዩ ተፈፃሚነት እንዲያገኝ፤ ይህ ካልሆነም በቻሪቲ ኮሚሽንም ሆነ በፍርድ ቤት በኩል የአባላትን መብት ለማስከበር የሚደረገውን እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ ይህ ጉባኤ እንደሚደግፈው እንደገና ለማረጋገጥ እንወዳለን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule