• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እባካችሁ ይህንን “ኢትዮጵያዊነት” አክብሩት!!

October 22, 2012 09:52 pm by Editor 1 Comment

ኢትዮጵያዊነት ከአጭበርባሪነት፣ ከሸፍጥ፣ ከሴራ፣ ከኩርፊያ፣ ከበቀል፣ ከተንኮል፣ ከደባ፣ ከድብቅ ዓላማ፣ ከአድማ፣ ከባንዳነት፣ ከአቃጣሪነት፣ ከከሃዲነት፣ ከተቀጣሪነት፣ ከማወናበድ፣ በተለይም ከማስመሰለና ከተራ የፖለቲካ ንግድ በላይ መሆኑንና ማንም ሊበርዘው ቢደክምም ሊሸረሽረው የማይችለው የልብ ማህተም መሆኑን ሰሞኑን አየን።

ባለፈው ሳምንት የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግርኳስ ቡድን ድል እውን ይሆን ዘንድ ሠንደቅ ዓላማቸውን ለብሰው ሌሊቱን ሙሉ ላገራቸው ያዜሙ፣ በየቤታቸው ሆነው በጸሎት የማለዱ፣ በመላው ዓለም በየድረገጹ የመልካም የደስታ ምኞታቸውን ሲገልጹ የነበሩ፣ በዋናው የትግል ሜዳ የአገራቸውን መለያ ለብሰው ታሪኩን ያከወኑና የትግሉን ስትራቴጂ በመንደፍ ታሪክ የሰሩ ድርና ማግ ሆነው አገራቸውን አብርተዋታል።

ብንዘገይም ለመላው የኢትዮጵያ እግርኳስ ቡድን አባላት፣ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብና አፈጣጠሩ ጤነኛ ባይሆንም ለፌዴሬሽኑ አመራሮች እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን። በአፍሪካ ዋንጫ ብቁ ተፎካካሪ የመሆናችን ጉዳይ እንዳለ ሆኖ፣ ከሰላሳ አንድ ዓመት በኋላ ለዚህ ታላቅ ዕድል መብቃት አዲሱ ትውልድ የረሳቸውን አህጉራዊ ታሪኮቻችንን እንዲያወቅ ረድቶታልና ደስታችን ወደር የለውም። ድሉን ተከትሎ የመንግስት ባለሥልጣናትና የስፖርት ጋዜጠኞች የግል፣ የመንግስት ሳይባሉ ሲያሰሙ የነበረው ቡራ ከረዩ ግን አሳዝኖናል። ፕሮፓጋንዳው እስኪያቅለሸልሸን ድረስ ተጠይፈነዋል። ምክንያቶቻችንን እናቅርብ።

የኢትዮጵያ ስፖርት እንቅስቃሴ ከሩጫው በስተቀር ሙሉ በሙሉ ሞቷል። ሩጫው በውስን አትሌቶች ትከሻ ላይ ተንጠልጥሎ ቆይቶ የለመድነውን የአስር ሺህ ድል ሙሉ በሙሉ ማስከበር እንኳን ተስኖናል። ቤቱ በሙስናና በህገወጥ አሰራር መጠቃቀሚያ መሆኑን ጸረ ሙስና ኮሚሽን የፈረደበት ነው። ሌሎቹ ፌዴሬሽኖችም የሚወራ ዜና የላቸውም። እግር ኳሱም አንዴ ኩዴታ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ ብር አለን የሚሉ የአገራችን ባንኮች ቁጥር አንድ ተበዳሪዎች ጀሌ እየኮለኮሉ የሚነዱትና የሚክቡት፣ በብልሹ አሰራር፣ በሙስናና በብክነት የተመደበ ተቋም ነው።

ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴን ጨምሮ በአገሪቱ ያሉት ከሃያ አንድ በላይ ፌዴሬሽኖችና የስፖርት ማኅበራት ሙሉ በሙሉ የሚመሩት ስለስፖርቱ ምንም እውቀት በሌላቸው ካድሬዎችና የመንግስት ባለስልጣናት መሆኑ የአገሪቱን ስፖርት እንደገደለው በጥናት ተረጋግጦ ሳለ አሁን የተገኘውን ድል የአገሪቱ የስፖርት ፖሊሲ ውጤት ተደርጎ ለፖለቲካ ንግድ ስራ ሲውል አገር ውስጥ ያሉትም ሆኑ ከአገር ውጪ የሚገኙ ሚዲያዎች አብረው ማጫፈራቸው ያሳዝናል። ሚዲያ አብሮ ሲያብድ ጉዳቱ የከፋ ነውና እናስተውል ለማለት እንወዳለን። ቢያንስ ቢያንስ መንግስት በየመንደሩ የነበሩ የመጫወቻ ሜዳዎችን በሊዝ ጨረታ ለወዳጆቹ እየቸበቸበ ታዳጊዎችን መጫወቻ በማሳጣት አደገኛ ቦዘኔ በማለት ለአደገኛ ሱስ መዳረጉ ያስጠይቀዋል።

ደስታን መግለጽ አንድ ነገር ሆኖ ሳለ፣ ደስታው ስፖርቱ በደረሰበት ድርሽ የማይሉት የአቶ መለስ “አርቆ አሳቢነት” ውጤት እንደ ሆነ አድርጎ ኢቲቪ ማቅረቡ ከተለመደው የኢቲቪ ፕሮፓጋንዳ የተለየ ባለመሆኑ አያስገርምም። “የባንዲራ ቀን” ለማክበር በህይወት ዘመናቸው አንድ ቀን ለዚያውም ለሰላሳ ደቂቃ ስታዲየም የተገኙትን አቶ መለስን ባልዋሉበት ቦታ መሰንቀር የሙያም ስነ ምግባር አይመስለንም። ያለ ምንም ማጋነን መለስ ለስፖርቱ ካላቸው ደንታ ቢስነት አንጻር አዲስ አበባ ስታዲየም መሰቀላቸውም አግባብ አይደለም እንላለን። በተስፋ አገርና መላውን ስፖርት ቤተሰቦችን በኦርኬስትራ የሚያታልሉት የሼኽ መሃመድ ሁሴን አላሙዲን ጨምሮ!!

ላለፉት ሃያ አንድ ዓመታት ለታዳጊ ህጻናት ፕሮጀክት ስልጠና ከፊፋ የተላከ የርዳታ ብር ተዘርፏል። ሰልጣኞች ኳስና ጫማ የሚገዛላቸው በማጣት ሲበተኑ አቶ መለስም ሆኑ የስፖርት ሚኒስትሩ የፈየዱት ነገር አልነበረም። ተጠሪነቱ ለአቶ መለስ የሆነው የጸረ ሙስና ኮሚሽን አበጥሮ ያቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ እንዲተገበር አላደረጉም። ስታዲየም እንዲሰራ ሲጠየቁ ተዛልፈው እንደነበር አይረሳም። አሁን ስታዲየም ይሰራበታል የተባለውና ከበሮ የሚመታበት ሜዳም ድሮ በ1974 ኮሎኔል መንግስቱ ብሔራዊ ስታዲየም እንዲሰራበት በስጦታ የሰጡት ቦታ መሆኑ እየታወቀ እስአከሁን አለመሰራቱ አጀንዳ መሆን ሲገባው እንደ ታላቅ ስኬት መቅረቡ ሊዋጥልን አይችልም። የዛሬ 60ዓመት በተሠራ ስታዲየም ቡድናችን ከ31ዓመት በኋላ ለድል በቃ ሲባል ከዚህ ለድል ካልበቃንባቸው ዓመታት ውስጥ ኢህአዴግ ሃያ አንዱን ይወስዳል – 70በመቶ ማለት ነው፡፡

ሚዲያ መረጃ አቀባይ ቢሆንም ብሔራዊ ስሜትን በተመለከተ የሕዝብ አካል እንደ መሆኑ ያንን መካፈሉ ስህተት ባይኖረውም ዋናውን ጉዳይ ግን መርሳት የለበትም፡፡ ድልን ሲያበስርና ችቦ ሲለኩስ ስኬት ዓልባ የነበሩትን ዓመታት ማስታወስና መጪው ደግሞ ምንያህል ፈታኝ ሊሆን እንደሚችል በሰከነ መንገድ የማስገንዘብ ኃላፊነቱን መዘንጋት አይገባውም፡፡ በቀጣይ ጨዋታዎች ላይ ያለንን ብቃትና ተወዳዳሪነትም ሳይጠቁም በድል ብቻ የሰከረ ሚዲያ በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ያሉት ከሚያደርጉት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ የተለየ አያደርገውም፡፡

በድሉ የተደሰትነውን ያህል በድሉ አማካይነት የሚፈጸመውን የታሪክ ሽሚያ አልወደድነውም።ኢህአዴግ ተራ የፖለቲካ ቁማሩን በመተው ይህንን ከባድሜ ዘመቻና መለቀቅ በኋላ የታየውን ሊደበዝዝ የማይችል ብሔራዊ ስሜት ትምህርት ይውሰድበት – መማር ከቻለ፡፡ ኢህአዴግ እንደሚለው ኢትዮጵያዊነት “በአየር ላይ” ያለ ባዶ ስሜት ሳይሆን በእያንዳንዱ ዜጋ ልብ ውስጥ የታተመ ውድ ጉዳይ ነውና ይኩራበት፤ አሁንም ድል ለኢትዮጵያ ህዝብና ለቡድናችን!! ለቀጣዩ ውድድር ልዩ ወገብ ጠበቅ!!

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. dereje melaku says

    October 25, 2012 11:33 pm at 11:33 pm

    dear the children of Ethiopia

    first and for most i would like to thank you so much for your relentless effort to give information for the Ethiopian people. having said that let me introduced my self this is … who was the member of the veteran Ethiopian teachers association ,Ethiopian free press association and i was also a columnist in tobia and lissane hezebe private news paper , currently i am a columnist in finotenessanet newspaper

    i have been a member of the Ethiopian human rights council for the last 15 years and currently i am one of the executive members of Ethiopian human rights council

    by the way i have got your web site while i was coming in Ireland for a very short period of time internship program me but when i return back to Ethiopia it is impossible to get your web site as that of Ireland so that how could have access to your web site in Ethiopia ? can you subscribe your web site to my web site to my email ? please help me to read your lovely web site as you know it all web site which focused on the poltics of Ethiopia off course which is independent one banned by the facist wouyane regime so that we do not have alternative source of information . if possible subscribe your very important web site to me and my friend

    with best regard
    your sincerely dm

    WE LOVE ETHIOPIA AND WE STAND FOR HER UNITY

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule