• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ፎቶና ታሪኩ

November 16, 2017 08:30 pm by Editor Leave a Comment

በወያኔ ዘመን በህወሃት ቀንበር
ያሳለፍነው ህይወት የጠጣነው አረር
እንዴት እንደሆነ እንዴት እንደነበር
ጠበቃ ከማቆም እማኝ ከመደርደር
ይኸው የኛ ፎቶ ታሪኩን ይናገር።

*የተከበርክ አንባቢ ሆይ! ቀጣዮቹን ፎቶዎች በፅሞና እና በማስተዋል ተመልከታቸው፤ መልዕክቶቹንም ረጋ ብለህ ወደ
ነፍስህም ቀርበህ አንብብ። ምናልባት ለመፍትሄውም ሆነ ለችግሩ አንተ ትቀርብ ይሆናልና።

የድህነት ጠባሳዎቸ ከሚታዩባቸው የጎንደር መንገዶች አንዱ (ፎቶ: James Jeffrey/IPS)

በጎንደር ከተማ የሚታየው ዘግናኝ የቁልቁለት ‘እድገት’። በህወሃት በይፋ ጠላትነት ተፈርጆ የቁም ስቅሉን እያየ በሚገኘው የአማራ ህዝብ ላይ ሆን ተብሎ በመካሄድ ላይ ያለው የኢኮኖሚ ተዐቅቦ ያስከተለው መከራና ድህነት እጅግ ዘግናኝ ሲሆን በቅርቡ በወጣ ጥናታዊ ዘገባም የአማራ ህፃናት ከዚህ በፊት ታይቶ በማያውቅ ሁኔታ (በርግጠኝነትም በሌሎች ክልሎች በዚህ ስፋትና መልክ ያልተከሰተ) ያለ ዕድሜያቸው እየቀነጨሩ በመሆኑ ክልሉ ሰፊ የሆነውን የነገውን የሥራና የአስተዳደር ተረካቢ የሆነውን ወጣት ሀይል የማጣት እድሉ ከፍተኛ እንደሆን ተጠቁሟል። ጎንደርና ባህር ዳር ሲጨልም መቀሌና አክሱም በብርሃን ያንፀባርቃሉ። በአማራው ክልል ባለፈው የህወሃት ሩብ ምዕተ ዓመት አገዛዝ የጤና ጣቢያዎች ሆስፒታሎች መንገዶች ት/ቤቶች የመብራትና የውሃ መስመሮች ሆን ተብለው እንዳይገነቡ የነበሩትም እንዲወላልቁና እንዲፈራርሱ የተደረገበት የክፉ ሰዎች በቀለኝነት በህዝብ ሰቆቃና ህይወት መጠነ ሰፊ ጥፋት ያደረሰና እያደረሰም ያለ የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር ዘር የማጥፋት ተልዕኮ ውጤት ነው።

በአማራው ክልል በሩብ ምዕተ ዓመት የተገነቡት ከባድ ኢንዱስትሪዎችም ሆኑ መጠነኛ ስንት ናቸው? የአማራው ክልል ካለው የቆዳ ስፋትና በውስጡም ከሚኖረው ህዝብ ብዛት አንፃር በትግራይ ክልል የተገነቡት ከባድ ኢንዱስትሪዎችና መጠነኞችስ ስንት ናቸው? ንፅፅሩስ ተገቢና ፍትሃዊ አይሆንምን? ብአዴን ይህንን አያውቅም? ብአዴን እመራዋለሁ የሚለው ህዝብ ፍትሃዊ ባልሆነ ብቻ ሳይሆን ጭፍን በቀለኛ በሆነው ህወሃት ቀጥተኛ ብቀላ ሲፈፀምበት መሬቱን ሲገፈፍ ንብረቱን ሲቀማ የመኖር ህልውናው በየአቅጣጫው በእሾህ ተከቦ ሲደማ፤ በትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር የአጥፍቶ ጠፊ ሰላዮችና በተባባሪዎቹ የዘር ድርጅቶችና አስፈፃሚ ታጣቂዎች በመላው ሀገሪቱ ደሙ ደመ ከልብ ሲሆንና ‘የድረሱልኝ’ ጣዕር ሲያሰማ እንዴት ሆኖ ነው ብአዴን ከአማራው አብራክ የወጣ ነው ማለት የሚቻለው? ብአዴን ሆይ! ሁለት ሞት የለምና አንዱንና ሰማዕታዊውን ሞት መርጠህ ለህዝብህና ሰው ስለመሆን ስትል ዘር አጥፊውን ህወሃት ተጋፍጠህ ብትሞት እንኳን ሞትክ አይባልምና አደባባይ ወጥተህ ህዝብህን ምራ! ወይም ለሀገራቸው ኢትዮጵያና ለሚወክሉትም ህዝባቸው ለመሞት ለተነሱ ትንታጎች የአማራ ውልድ ወጣት የኢትዮጵያ ልጆች አስረክብ!! ብአዴን ሆይ ስማ፤ ሁለት እግር አለኝ ብሎ ሁለት ዛፍ በተመሳሳይ ጊዜ መውጣት አይቻልም። ወይ የህወሃት ናዚስቶችን ወይ ህዝብህን ሀገርህን ኢትዮጵያንና ፍትህን ምረጥ፤ ይኸው ነው!

በፌዴራል መንግሥት ልዩ ልዩ በጀትና ወጪ በከፍተኛ ፍጥነትና ዕድገት በመገንባት ላይ ያለችው መቀሌ ከተማ (Wikimedia Commons)

ባለፈው ሩብ ምዕተ ዓመት በትግራይ ክልል የተካሄደው ልማትና ያስከተለው ለውጥ በመላ የኢትዮጵያ ግዛቶች ተካሂዷል ከተባለው ልማት ግንባታና እድገት በእጥፍ ድርብ የሚበልጥ ነው። ዘመናዊ የህዝብ ማመላለሻ አውሮፕላኖች የካርጎና የጦር ጄቶች ማሳረፊያ ጣቢያዎች እጅግ የተራቀቁ ሆስፒታሎችና በአቅርቦት የተደራጁ አያሌ ጤና ጣቢያዎች መንገዶች የተሟላ የመብራት አገልግሎት ፋብሪካዎችና ኢንዱስትሪዎች የንፁህ ውሃ መስመሮች የተደራጁና የተሟሉ ትምህርት ቤቶች ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች እና ወዘተርፈዎች ሁሉ ከተከዜ በታች ባለው ግብር ከፋይ የኢትዮጵያ ህዝብና በሀገሪቱ አንጡራ ሀብት ኪሳራ በአንዲት ክፍለሀገር ላይ ተገንብተውና በመገንባትም ላይ የሚገኙ ሲሆን ይህ ሁሉ አደሏዊነትና ግፍ የሚፈፀመው ደግሞ ‘ትግራይ እስክትለማ ሌላው ይድማ” በሚለው የዘረኛው ህወሃት በቀለኛ መርህና በተባባሪዎቹ የሥልጣን አጎብዳጅነትና አሽከርነት ነው። ከተከዜ በታች የሚኖረው ኢትዮጵያዊና አዲስ ትውልድ አፍ መፍቻው ‘መብራት የለም፤ ውሃ የለም፤ ስኳር የለም፤ ሥራ የለም…’ ሲሆን በትግራይ ክልል በሚኖሩ ትግራውያን እኒህ አፍ መፍቻና የእለት ተእለት መግባቢያ ቃላት አይታወቁም። ወደ ሶስት አሥርታት እየተጠጋ የሚገኘው የህወሃት ፌዴራሊዝም ውጤት የኢፌዲሪ እኩልነት። ድንቄም እኩልነት!

መስፍን ማሞ ተሰማ

(ቀሪዎቹን ፎቶዎችና ታሪካቸውን ለማንበብ እዚሀ ላይ ይጫኑ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule