• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አስደሳቹ የብሔራዊ ቡድን ውጤትና ቅሌት

October 31, 2012 08:30 am by Editor 2 Comments

ባሳለፍናቸው ሳምንታት  እሁድ ዕለት አንበሳው የብሔራዊ ቡድናችን ያደረገው ለአፍሪካ ዋንጫ የማለፍ ትንቅንቅ በጣም አጓጊና አስደሳች እንደነበር አይተነዋል።  ጀግናው ብሔራዊ ቡድናችን የሱዳን አቻውን  ሁለት- ለዐልቦ  በሆነ ውጤት በዝረራ አሸንፎ እነሆ ከሰላሳ አንድ አመታት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ እንድናልፍና  ልክ  አረንጓዴ ጎርፍ ተብለው የሚጠሩት አትሌቶቻችን ሰንደቅ ዓላማችንን ከፍ አድርገን እንድናውለበልብ እንዳደረጉን ሁሉ ዛሬም ብሔራዊ ቡድናችን አፍሪካ ላይ ለጊዜውም ቢሆን መሀሉ ላይ የሰይጣን አምልኮት ምልክት ያለበትን ባለኮከቡን አረንጓዴ ፥ ቢጫና ፥ ቀዩን ሠንደቅ ዓላማችንን እንድናውለበልብ አድርገውልናል፡፡ ምስጋና ይግባቸው ለዋልያዎቹ።

ይህን ድል አቶ መለስ በህይወት ኖረው ቢያዩት ደስ ይለኝ ነበር። የሚሉትን ለመስማት፡፡ ግን አፈር ይክበዳቸውና የሉም። ሀገራችን ኢትዮጵያን እግዚአብሔር አምላክ በቸርነቱ እንደሚጠብቃት ብዙ ምልክቶችን አሳይቶናል። ለዚህም ለአብነት ያህል፦ አዲስ አመት መግቢያ ግድም ዘረኛውንና አምባ ገነኑን፤ እንዲሁም ለኢትዮጵያ ህዝብ ምንም አይነት ደንታ የሌለውን፥ ህዝቡን በዘር የከፋፈለውን ፥ አረመኔ መሪ መለስ ዜናዊንና ቋሚ የሲኖዶስን ህግ ጥሶ በአጉራዘለልነት  በራሱ ፈቃድ የሾማቸውን ጭፍራውን አባ ጳውሎስን ጨምሮ ከምድረ ገዕ እንዲጠፉ አድርጓቸዋል። ሎሚ ተራ ፥ ተራ ነውና ሌሎቹንም ተራ በተራ  እንደሚጠርጋቸው አልጠራጠርም፡፡ በቅርብ የምናየው ይሆናል ።

ለሃያ አንድ ዓመታት ግራ – ሸቅብ ብለው በሃገሪቷ ላይ የጨበጠትን መዳፋቸውን አዲሱ አመት አስፈልቅቆ ጠላቶቿን ስለቀነሰላት  አዚማቸው ከሽፎ ፣ ብሄራዊ ቡድናችን ብቻ ሳይሆን ፥ የወጣት ቡድኑም ሆነ ፥ የሴቶቹ ሉሲ የእግር ኳስ ቡድን ጭምር ኢትዮጵያን ወክለው በአፍሪቃ ውድድሮች ውስጥ ዘንድሮ እንዲካተቱ አምላክ ፈቅዷል ፡፡

በቅድሚያ ግን ለስፖርት ቤተሰቦችና ለመላው የኢትዮጵያ ስፖርት አፍቃሪ ህዝብ  በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ እላለሁ ። መጨረሻውንም እንዲያሳምርልን እየተመኘሁ ፣ አንድ ቅር ወደተሰኘሁበት ጉዳይ ላይ ግን በቀጥታ ላምራ ፡፡ ድሉን ያስጨበጡን ዋልያዎቻችንና  የወቅቱ የብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝን ጨምሮ፣  ለጋዜጠኞች የሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ግን እጅግ አስተዛዛቢ ነበር ፡፡ እማን ላይ ቆመሽ ማንን ታሚያለሽ ሆኖባቸው እንደሆነም ልቦናዬ ጠንቅቆ ያውቃል ፡፡  ልማታዊ እስፖርተኝነትና የካድሬ ሥራ ሆኖባቸው ተጫዋቾቻን ፣ አቶ መለስ በህይወት ዘመናቸው የኢትዮጵያ የግር ኳስ ቡድን ላይ የተዛበቱትን በመርሳት መታሰቢያነቱ ለአቶ መለስ ይሁንልን ማለታቸው ግን አንጀቴን  ነው ያቃጠለው ።

መሬት ይቅለላቸውና ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ እንኳንም በዚህ ዘመን  ያልኖሩ ፡፡ በህይወት ቢኖሩ ኖሮ ኳስ ተጨዋች አይብቀልብሽ ብለው አገሪቷን ይረግሟት ነበር ፡፡  አቶ መለስ በአንድ ወቅት ስለ ብሔራዊ ቡድናችን ተጠይቀው የመለሱትን መልስ ላስታውሳችሁ ፡፡ በዚያን ወቅት  አቶ መለስ የጦር ኃይላችንን ወደ ሶማሌ ለማዝመት ደፋ ቀና የሚሉበት ወቅት ነበር ፡፡ አንድ ጋዜጠኛ ፦ ወደ ሶማሌ ተልኮ የሄደውን የኢትዮጵያ ወታደር እንደከዚህ በፊቱ አሜሪካዊ ወታደር  ሬሳውን በመኪና ሲጎትቱት  የኢትዮጵያ ህዝብ ቢያይ ምን የሚልዎት ይመስሎታል ? ብሎ ለጠየቃቸው ጥያቄ  የመለሱት መልስ ፦ ለጦርነት የሚሄደው እኮ ጀግናው የኢሕአዴግ ሠራዊት እንጂ የኢትዮጲያ ብሔራዊ ቡድን አይደለም በማለት አሳዝነውናል።

በሌላ ወቅት ደግሞ ብሔራዊ ቡድናችን ከሀገር ውጪ ሊጫወት ሄዶ በሙሉ ተጫዋቾቹ ሳይመለሱ ቀሩ ተብለው ሲጠየቁ ፦ መንገዱን ጨርቅ ያርግላቸው ይህ እኔን አያሳስበኝም ፡፡ እኔን የሚያሳስበኝ አንድ ገበሬ ቢጠፋ ነው ብለው መልሰዋል።  እንደውም ስታዲየሙን ቢለቁልን ማዳበሪያ ፋብሪካ እንከፍትበታለን በማለትም ጭምር በብሄራዊው ቡድን ላይ ተዛብተውበታል ፡፡  ታዲያ እንግዲህ ጎበዝ ለዚሁ በብሔራዊ ቡድናችን ላይ በሞራሉ የተረማመደበትንና በቡድኑ አናት ላይ ቀለበት መንገድ የሰራበትን መሪ ነው መታሰቢያነቱ ለሱ ይሁን ብለውአሰልጣኝና ተጨዋቾች ያስደመሙን።

ማን ያውቃል ! ከእጅ አይሻል ዶማ እንዲሉ አቶ ሀይለማሪያምና ጭፍሮቻቸውም አስገድደዋቸው ይሆናል ስፖርተኞቻችን ልማታዊ ስፖርተኞች የሆኑብን ፡፡ እንደኔ እንደኔ ግን መታሰቢያነቱ ለአቶ ይድነቃቸው ተሰማና ቤተሰቦቻቸው እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ እግር ኳስ አፍቃሪ በሙሉ ቢሆን በጣም ደስ ይለኝ ነበር ግና አልሆነም ። እንግዲህ ገዢው የኢሕአዴግ ፓርቲ ሲገረሰስና ሙሉ ለሙሉ ከስልጣን ሲወገድ የብሔራዊ ቡድናችን ዝናና ክብረ ሞገስ ልክ እንደ ሶስተኛው የአፍሪቃ ዋንጫ ጀግንነታችን መመለሱ አይቀርም ፡፡ ጅምሩንም በዚህ አዲስ አመት አይተናልና ፡፡ ለአለም ዋንጫም አገራችን እንደምትደርስ አንጠራጠርም ፡፡  ያኔ ታዲያ ማስታወሻነቱ ለማን ይሆን ? ቸር እንሰንብት ።

ውድቀት ለወያኔና ጭፍሮቹ እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ !!
ዳዊት አበበ / ኦስሎ ኖርዌይ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Comments

  1. elias bekele says

    November 1, 2012 01:50 am at 1:50 am

    bertu

    Reply
  2. እስከመቼ says

    November 1, 2012 11:40 pm at 11:40 pm

    ወንድሜ ዳዊት አበበ ከኖርዌይ፤
    ጥሩ ብለሃል።
    የእግር ኳስ ቡድናችን ባደረገው ጉዞ የተሰማን ደስታና ያሳየነው ፍንደቃ፤ የአንድነት ምንነታችን መግለጫ ነው። አንድነታችን የተደበቀ፣ የማይታይ፣ የተሰረዘ፣ ወይንም የጠፋ አይደለም። አንድነታችን በውስጣችን ያለ ሀቅ ነው። ብቅ የሚለው ሲፈተን ነው። የእግር ኳስ ቡድናችን ለረጂም ዘመን ርቆት ከነበረው የአፍሪካ ዋንጫ ድግስ መግባቱ፤ ሁላችንንም ቀሰቅሰን። አንድነን ብለን ዓይናችንን አፈጠጥን። ጠላት መጣ ሲባል፤ ያለ የሌለውን መሳሪያ አንግቦ፤ ካገኘው ኢትዮጵያዊ ጋር ባንድነት ተሠልፎ፤ ሀገሩን ለመከላከል እንደሚነሳው ሁሉ፤ አንድነን ብለን ተነሳን። በአንድነታችን ኮራን። ፈነደቅን። ዘርዓይ ድረስን፣ አቡነ ጴጥሮስን፣ በላይ ዘለቀን፣ ባልቻ አባ ነፍሶን፣ ገብርዬን፣ ሽብሬ ደሳለኝን፣ እቴጌ ጣይቱን፣ ዘርዓያቆብን፣ አበበ በቂላን፣ ፋጡማ ሮባን፣ አቢቹን፣ የኛ ብለን ባቀፍነው እጆቻችን፤ የአባይን ወንዝ፣ የአዋሽን ወንዝ፣ የራስ ደጀንን ተራራ፣ የአክሱምን ሀውልት፣ የላሊበላን ገዳም፣ ሶደሬን፣ ኦሞን፣ የኛ እንዳልነው ሁሉ፤ ኮራንባቸው፤ የኛ ብለን አቀፍናቸው። ምንም እንኳ ማስታወሻነቱን ያሉት ባለሥልጣናት ለፈለጉት ቢሠጡትም፤ ማስታወሻነቱ እስከዛሬ በእግር ኳስ ታሪካችን አስተዋፅዖዋቸው ከፍ ላሉት ለይድነቃቸው ተሰማ፣ ለነመንግሥቱ ወርቁ መሆኑን ነጋሪ አንፈልግም። የተለጠፈው ማስታወሻ ይቀረፋል።
    ወደፊት የበለጠ እንጠብቃለን
    የወደፊታችን ያማረ ነው
    ወያኔን አያካትትምና
    እስከመቼ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule