• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ጦርነት የሲዖል ተምሳሌት ነው” የኖቤል የሰላም ሎሬት ጠ/ሚ/ር ዐቢይ

December 10, 2019 03:55 pm by Editor Leave a Comment

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በኖርዌይ፣ ኦስሎ የኖቤል የሰላም ሽልማታቸውን ከተቀበሉ በኋላ ካስተላለፉት መልዕክት የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች፤

• የኖርዌይ የኖቤል ኮሚቴ ለሰጠኝ እውቅና አመሰግናለሁ

• ለኢትዮ-ኤርትራ የሰላም ስምምነት የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የሰላም ቁርጠኝነት ወሳኝ ነበር

• ይህንን ሽልማት የምቀበለው የአፍሪካ እና የዓለም ህዝቦችን ወክዬ ነው፤ በኢትዮጵያውያን እንዲሁም በኤርትራውያን እና በኢሳያስ አፈወርቂም ስም ነው

• እዚህ የደረስኩት በብዙ ጦርነት ውስጥ አልፌ በዕድል ነው፤ ይህን ሳያዩ ያለፉ ብዙ ናቸው፤ ከ20 ዓመታት በፊት በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት የሬድዮ ኦፕሬተር ነበርኩ

• የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት በርካታ ቀውሶችን አስከትሏል፤ ከ100 ሺህ በላይ ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች ተፈናቅለዋል፤ የንብረት መውደምም አጋጥሟል

• ሁለቱ ሀገራት ለሁለት አሥርት ዓመታት ጦርነትም ሰላምም በሌለበት የውጥረት ሁኔታ ውስጥ ቆይተዋል፤ በዚህም በርካታ ሰራዊት በሁለቱ አገራት ድንበር መሽጎ ቤተሰቦች ሳይገናኙ ቆይተዋል

• ከ18 ወራት በፊት ወደ ሥልጣን ስመጣ ለዚህ እልባት መስጠት በጣም አስፈላጊ ሆኖ አገኘሁት

• ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጋር ተገናኝተን ሁለቱ አገራት ጠላቶች እንዳልሆኑ ይልቁንም የጋራ ጠላታችን ድህነት እንደሆነ ተስማምተን ለአገራቱ እና ለቀጠናው ብልፅግና መስራት ጀመርን፤ እናም አሁን በሁለቱ ሀገራት መካከል ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሰፍኗል

• ሰላም የመኖር መንገድ፣ ጦርነት የሞት መሠረት ነው የሚል እምነት አለኝ፤ ሰላም በቤተሰብ፣ በጎረቤት፣ በመንደሮች፣ በከተማዎች፣ በሕዝቦች መካከል ያስፈልጋል፤ በዜጎቻችን ልብ ውስጥ ሰላም፣ ፍቅር እና እርቅ ልንዘራ ይገባል

• የኔ የሰላም ራዕይ በመደመር ፍልስፍና ላይ የተመሠረተ ነው፤ መደመር አገር በቀል ሀሳብና የጋራ ብልጽግና ላይ ያተኮረ ፍልስፍና ነው

• የመደመር ጽንሰ ሀሳብ እንደ ዘር ውስጤ የበቀለው በኦሮሚያ ክልል በምትገኝ የትውልድ መንደሬ በሻሻ ውስጥ ነው

• የመደመር ፍልስፍና ብዝሃነታችን የኢትዮጵያችን ውበት ነው፤ እኔ የወንድሜ እና የእህቴ ጠባቂ ነኝ፤ “አንተ በሰላም እንድታድር ጎረቤትህ በሰላም ይደር” የሚል እሳቤን የያዘ ነው

• በመደመር ጽንሰ ሀሳብ ውስጥ እኛና እነሱ የሚባል ነገር የለም

• ኢትዮጵያውያን በአንድነት በመቆማችን ለዓመታት ነፃ አገር ሆነን ቆይተናል

• የአፍሪካ ቀንድ የአሸባሪዎች ቀጠና እንዲሆን አንፈልግም፣ የሰላም ቀጠና እንጂ

• ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በሰላም ላይ ኢንቨስት ማድረግ ይጠበቅበታል

• የፖለቲካ እስረኞችን ፈትተናል፤ ለዓመታት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሲካሄድባቸው የነበሩ እስር ቤቶችን ዘግተናል፤ ለዴሞክራሲ ግንባታ መንገድ ጠርገናል፤ በቅርቡ ነፃና ፍትሓዊ ምርጫ እናካሂዳለን

• ለሁሉም ዜጎቿ እኩል ፍትሕ እና እኩል መብት የምትሰጥ ሀገርን እጅ ለእጅ ተያይዘን እንድንገነባ ለኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ጥሪ አቀርባለሁ

© EBC

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: abiy ahmed, Nobel Peace Prize Laureate Abiy Ahmed Ali, Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule