• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአዲስ አበባ ውሃ እስከ 20ቀናት ይጠፋል

March 16, 2014 11:44 pm by Editor 2 Comments

* “የውኃ ምርት ችግር የለብንም የኤሌክትሪክና የማሰራጨት እንጂ” የውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን

የፌዴራል መንግሥት መቀመጫና የአፍሪካ መዲና በሆነችው በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ፣ ለሁለትና ሦስት ቀናት ይጠፋ የነበረው የውኃ ችግር እስከ 20 ቀናት እየጠፋ  መሆኑንና ችግሩ ተባብሶ መቀጠሉን ነዋሪዎች እየገለጹ ነው፡፡

በተለይ ከሳሪስ እስከ ቃሊቲ፣ አየር ጤና፣ ወይራ ሠፈር፣ ለቡ፣ ጉለሌ፣ ኮልፌ ቀራኒዮ፣ ፒያሳ፣ ሽሮ ሜዳ፣ መርካቶ፣ የካ በተለያዩ ወረዳዎች አራት ኪሎ (አልፎ አልፎ) በአጠቃላይ በከተማው ከአምስት እስከ 20 ቀናት ውኃ ጠፍቶ እንደሚሰቃዩ ገልጸዋል፡፡ ወ/ሮ ስንታየሁ አበበ የተባሉ የሳሪስ አቦ ማዞሪያ አካባቢ ነዋሪ እንደገለጹት፣ የውኃ ችግር ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መምጣቱ ያስገርማቸዋል፡፡ ቀን ቀን ይጠፋና እኩለ ሌሊት ይመጣላቸው በነበረው ውኃ ሲማረሩ፣ ይባስ ብሎ የመጥፋቱ ሁኔታ ወደ ሦስት፣ አራትና አምስት ቀናት አድጐ አሁን እስከ 20 ቀናት ውኃ እንደማያገኙ ጠቁመዋል፡፡ በመንገድ ግንባታ ምክንያት በሚል በተለይ ከ2001 ዓ.ም. እስከ 2004 ዓ.ም. መጀመርያ ወር ድረስ በፈረቃ በሁለትና ሦስት ቀናት ቆይታ ያገኙት የነበረው ውኃ፣ መንገዱ ከተጠናቀቀ በኋላ ብሶበት ወደ ወር ሊቃረብ መድረሱንና አሁን ባለው ሁኔታ በቅርቡ ወር ሙሉ ላያገኙ እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡

መንግሥት ከፍታ ባላቸው አካባቢዎች ውኃ ማዳረስ እንዳቃተው አምኖ ሲገልጽ የከረመ ቢሆንም አሁን ግን በለገዳዲ፣ ገፈርሳና አቃቂ ቃሊቲ የከርሰ ምድር ውኃ አካባቢ ያሉ ነዋሪዎችም ውኃ እያጡ በመሆኑ ‹‹ምን ተፈጠረ?›› የሚል ጥያቄ እየተፈጠረባቸው መሆኑን ወ/ሮ ስንታየሁ ገልጸዋል፡፡ ቀደም ባሉት ጊዜያት ውኃና ኤሌክትሪክ  የሚጠፉበት ጊዜና ቀናት በመገናኛ ብዙኃን ይነገር እንደነበር ያስታወሱት ወይዘሮዋ፣ አሁን መንግሥት ሰልችቶት ይሁን አሳፍሮት ዝምታን መምረጡ እያሰጋቸው መሆኑን አክለዋል፡፡

ከመሀል አዲስ አበባ (ፒያሳ) ጀምሮ እስከ ዳር ከተማና አቀበት በሚባሉ አካባቢዎች የሚኖሩ ሁሉ እንደ ወ/ሮ ስንታየሁ ‹‹የውኃ ያለህ›› እያሉ ሲሆን፣ የውኃና ፍሳሽ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች፣ በክፍለ ከተማና እስከ ማዘጋጃ ድረስ እየሄዱ አቤት ቢሉም ምላሽ ሊያገኙ እንዳልቻሉ እየገለጹ ነው፡፡ ከሁለት ሳምንት በፊት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ድሪባ ኩማ ባቀረቡት የግማሽ በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ላይ፣ ውኃን በሚመለከት ያቀረቡትን ሪፖርት በተለይ በውኃ ችግር water lineውስጥ ያሉ ነዋሪዎች አምርረው እየተቃወሙ ነው፡፡ አንድ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የሽሮ ሜዳ ነዋሪ እንደገለጹት፣ ‹‹እኛስ መጣች መጣች ብለን ሌሊቱን ስንሯሯጥ መኖሩን ለምደነዋል፡፡ የኛ ዕጣ ፈንታ የደረሳቸው የመሀል ከተማ ነዋሪዎች ግን ያሳዝኑኛል፡፡ ይበልጥ ደግሞ ያዘንኩት የታደለ አገር በዘመናዊ መንገድ ማንኛውንም አቅርቦት እንደልቡ ሲቀርብለት፣ እኛ የውኃ ጥም ለማርካት ቦቴ መኪና እንደሚገዛልን እየተነገረን ነው፤›› በማለት የከንቲባውን ሪፖርት ተገቢ አለመሆኑን በመግለጽ ተቃውመዋል፡፡

አስተዳደሩ ትኩረት በመስጠት ከተንቀሳቀሰባቸው ተግባራት አንዱ የውኃ ምርትን መጨመር መሆኑን የገለጹት ከንቲባ ድሪባ፣ በአቃቂ ቃሊቲ 19 ጥልቅ ጉድጓዶች መቆፈራቸውንና 80 ሺሕ ሜትር ኩብ ውኃ ማምረት መቻሉን፣ በለገዳዲም 11 ጥልቅ ጉድጓዶች እየተቆፈሩ መሆኑን፣ ለገዳዲን በማስፋትና የድሬ ግድብን በማሻሻል የውኃ ማምረት አቅምን ወደ 195 ሺሕ ሜትር ኩብ ለማሳደግ የሚያስችል ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በአጠቃላይ ወደ 260 ሺሕ ሜትር ኩብ የሚጠጋ ውኃ ማምረት የሚያስችል ሥራ እየተሠራ መሆኑንና ሁሉም ሥራዎች ሲጠናቀቁ 610 ሺሕ ሜትር ኩብ የውኃ ምርት ከፍ እንደሚልም በሪፖርታቸው ከንቲባው አብራርተዋል፡፡

ነዋሪዎች ግን ሥራውና ዕቅዱ ወይም እንቅስቃሴው ከወረቀት ላይ እንደማያልፍ  በመግለጽ፣ የዕለት ጥማቸውን የሚያስታግሱበት መፍትሔ እንዲፈለግላቸው እየጠየቁ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን ግን በነዋሪዎቹ አቤቱታና ሮሮ አይስማማም፡፡ ‹‹የውኃ ምርት እጥረት የለብንም፣ ችግራችን የሥርጭት ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ የመንገድ ግንባታዎችና በተደጋጋሚ የኤሌክትሪክ መጥፋት ከፍተኛ ችግር እየፈጠረብን ነው፤›› ሲሉ የባለሥልጣኑ ኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ የሥራ ሒደት ባለቤት አቶ ሙሉጌታ ከምሴ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

ባለሥልጣኑ ችግር ያለባቸውን አካባቢዎች ለይቶ ማወቁንና ከፍተኛ ችግር አለባቸው የተባሉትን ንፋስ ስልክ ላፍቶ፣ ጉለሌ፣ የካና ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍላተ ከተማዎች ውስጥ ለሚገኙ ነዋሪዎች፣ ለተወሰኑት ጊዜያዊ የፕላስቲክ መስመር እየዘረጋ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አቀበት ለሆኑት ደግሞ በመከላከያ ኢንጂነሪንግ ያሠራቸውን ታንከሮች እየተተከለ መሆኑን፣ ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት ደግሞ ጄኔሬተር እየተገዛና የፀሐይ ኃይል ለመጠቀም ጥናት እየተካሄደ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ (ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. liku says

    March 17, 2014 07:28 am at 7:28 am

    It is really a shame to have water distribution problem in the capital city of Africa union head quarter And this a country which was boasting electric power distribution to neighboring countries

    Reply
  2. Tesfaye says

    March 17, 2014 12:27 pm at 12:27 pm

    It is now a month since we got clean water around Betel Hospital. Who will resign from his or her post because of this failure?? I know none!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule