• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሁላችንም አብረን ነጻ ካልወጣን ማንም ብቻውን ነጻ ሊሆን አይችልም!”

October 12, 2016 11:23 pm by Editor 1 Comment

ኢትዮጵያ ድንቅ አገር ናት። ይህ ማስደነቋ ደግሞ ከሕዝቧ መደበላለቅ ጋር ውበቷን እጅግ አጉልቶታል። ከዛሬ 40ዓመት በፊት የተጀመረው ጎሣ፣ ዘር፣ … ላይ ትኩረት ያደረገው ገዳዳ የግራ ፖለቲካ ኢትዮጵያ አላት የተባለውን የፖለቲካ ችግር ሲፈታ ሳይሆን ይበልጡኑ ሲያወሳስበውና ሕዝብን ግራ ሲጋባ እዚህ ደርሰናል። በዚያ ርዕዮት የተጠመቁ ሕዝብን ሲያስፈጁ እንጂ ለሕዝብ ጥቅም ሲያመጡ አልታዩም፤ በዚያ የጎሣ ፖለቲካ ጥርሳቸውን የነቀሉም እስካሁን የማይሠራ ነገር በመሞከር በሽታውን ለአዲሱ ትውልድ እንደ ስጦታ አስረክበውታል።

ለነጻነት በሚደረገው ትግል የሁሉም ኢትዮጵያ ወገኖች በአንድነት ብሶታቸው፣ ምሬታቸው፣ … ሊሰማ ይገባል እንጂ በተናጠል “ፍትህ ለኦሮሞ፣ ፍትህ ለአማራ፣ ፍትህ ለኦጋዴን፣ …” የሚለው አካሄድ የትም የሚያደርስ አይመስለንም፡፡ የተጨቆንነው ሁላችንም ነን፤ የትግራይ ተወላጆችንም ጨምሮ! የምንታገለውም ለሁሉም ኢትዮጵያዊ መሆን ይገባዋል፤ ትግራዮችንም ጨምሮ! “ሁላችንም አብረን ነጻ ካልወጣን ማንም ብቻውን ነጻ ሊሆን አይችልም!”

ትላንት #የኦሮሞአቢዮትና #የአማራተጋድሎ ዓለምአቀፍ የትብብር ሰልፍ በሎንዶን ተካሂዶ ነበር፡፡ በሰልፉ ላይ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የመጡ ወገኖች ይወክለናል የሚሉትን ሠንደቅ ዓላማ ይዘው ተቃውሟቸውን አሰምተው ነበር፡፡ የታየው ኅብረትና አንድነት ይበል የሚያሰኝ ነው፡፡ መፈክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ሊነገሩና ዓለም እንዲሰማው ሊደረግ ይችላል፡፡  በህወሃት ለ25 ዓመታት የተዘራውን ክፉ የጎሣ ፖለቲካ ማሸነፍ የግድ ነው፡፡ መነጋገር፣ መወያየት፣ አብሮ ሰላማዊ ሰልፍ መውጣት በይበልጥ ሊበረታታ የሚገባ ነው፡፡ ይህ ደግሞ የሁላችንም ቤት ስለምንላት ኢትዮጵያ በአንድነት እንድናስብ የሚረዳን ነው፡፡ የመደበላለቃችንን ውበት የምናይበት አስደናቂ ትዕይንት ነው፡፡

omoከዚህ ጋር ተያይዞ በትላንቱ ሠልፍ ላይ ከተሰሙት መፈክሮች መካከል “ህወሃት ወደ ትግራይ TPLF to Tigray” የሚለው መፈክር ወደፊት ልንኖርባት የምንመኛትን አገር ስዕል የማያሳይ ሆኖ ነው ያገኘነው፡፡ ከዚያም ሲያልፍ “ፍትሕ ለኦሮሚያ፣ ነጻነት ለኦሮሚያ፣ (Justice for Oromia, Freedom for Oromia) ፍትህ ለአማራ፤ ነጻነት ለአማራ፤ …” እየተባለ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ሲነገር የነበረው መፈክር ትብብርን የማያሳይ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ በተነገረው መፈክር መሠረት ኦሮሚያ፣ አማራ፣ ሶማሊያ፣ ኦጋዴን፣ ሲዳማ እና ጋምቤላ ብቻ ናቸው ፍትሕና ነጻነት የተጠየቀላቸው፡፡ በበርካታ ቀውስ ውስጥ ያለው የኮንሶ ወገናችንስ? የህወሃት ታጣቂዎች እጅግ በሚዘገንን መልኩ እጅና አንገታቸውን በገመድ አስረው ወደ አልታወቀ ቦታ የወሰዷቸው የሱርማ ወገኖቻችንሰ? ፍትህና ነጻነት አያስፈልጋቸውም? ሌሎቹስ? በዚህ ዓይነት አፈካከርስ ስንቱን የኢትዮጵያ ጎሳ ጠርተን ልንጨርሰው ነው?

ከሁሉ በላይ ግን “ህወሃት ወደ ሄግ (TPLF to the Hague)” ተብሎ በተነገረበት ሰልፍ ላይ “ህወሃት ወደ ትግራይ TPLF to Tigray” የሚለው መሰማቱ ጥቂትም ይሁኑ ብዙ ከእኛ ጋር ህወሃትን እየታገሉ ያሉ የትግራይ ወገኖቻችን አገር ማሳጣት ይሆናል ብለን እንገምታለን፡፡ የህወሃት ሹመኞች የትግራይ ህዝብ ህወሃት ነው፤ ህወሃት የትግራይ ሕዝብ ነው እያሉ የሚደሰኩሩትን ትክክል ነው የማለት ሆኖ ነው የተሰማን፡፡ በሰልፉ ላይ እንደተባለው ትግሉ ህወሃትን ለፍርድ ማቅረብ ነው እንጂ ወደ ትግራይ መወርወር ነው ብለን አናምንም፡፡ በህወሃት ልባቸው ቆስሎ ከአገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን በርካታ ነቀፋና መገለልን እየተቀበሉ ያሉትን ጥቂት የትግራይ ወገኖቻችንን ማሳዘንና መሸሸጊያ ማሳጣት መስሎናል፡፡ ለህወሃትም የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ጥሩ መጠቀሚያ መሆን መስሎ ተሰምቶናል፡፡

ስለዚህ የሰልፍ አስተባባሪዎች በእንደዚህ ዓይነት ጉዳዮች ላይ ጥንቃቄ ቢያደርጉ እንመክራለን፡፡ ወቅቱ “የፖለቲካ ተኩላነት” የሚጠይቅ ስለሆነ ወደፊት በየትኛውም የዓለም ክፍል በሕዝብ ስም በሚደረጉ ሠልፎች ላይ ይህንን መሰል መፈክር ከማሰማት መቆጠብ ተገቢ ነው ብለን እናምናለን፡፡ ታላቁ መጽሐፍ እንዳለውም “እንደ እባብ ብልህ” መሆን እያንዳንዳችን ይጠበቅብናል፡፡ ጥላችንና ትግላችን ከህወሃት ሥርዓት ጋር መሆን አለበት እንጂ ከአንድ የኅብረተሰብ ክፍል ወይም ጎሣ ጋር መሆን አይገባውም፡፡ ሥርዓቱን ስንታገል ከሥርዓቱ ጋር አልላቀቅም ብለው የሙጥኝ ያሉትን ምርጫቸው ወደሚፈልጉት እንዲሄዱ ያደርጋቸዋል፡፡ በኅብረተሰብ ክፍል ላይ ጥላቻን የሚያነሳሱ ተግባራትን ከመፈጸም መታቀቡ ለኢትዮጵያችን መልካም ነው፡፡

“ሁላችንም አብረን ነጻ ካልወጣን ማንም ብቻውን ነጻ ሊሆን አይችልም!” (ፎቶና ጥቅስ: አኢጋን)

smne banner


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ®” አቋም ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Lusif says

    October 14, 2016 06:59 pm at 6:59 pm

    All countries are being led and governed by ” ELITES “. Most elites are calculated narcissists.narrow ideologiest, partisan tyrants who always try to impose their groups’ mentality on other groups. They are fearful to the power of unified people and are cowards.
    In spite of this, no wonder the elites placed themselves in their particular corner and undermine each other. The elite dream is always how much he gets out of all the disunity and suffering of the people. Such group of people can never think of giving, instead they calculate how much they can get.
    Currently, our country is deep trouble. Innocent lives are being lost, way of life is in shambles, no more peace, only confrontations.
    Every where we see tribal leaders foul crying in the name of their respective tribe. How the Ethiopian people then triumph over tyranny.?
    The Ethiopian people particularly the youth has spoken. The Youth has already brought down the dividing wall that made it weak the last quarter of century.
    The so called ” Elites ” never paid attention to the call of the Ethiopian citizens. At this moment they seem struggling among each other.
    The struggle for freedom, equality, justice, and democratic way of life is underway. Each day it is getting fiercer and stronger.
    The Ethiopian elites were supposed to get together, forge a national agenda and strategy, creat a national center that can be ran and managed by national figures. Such inability of so called “Elites” is a dismal failure, tantamount to betrayal. To be honest, to me, it is like a treasion.
    Such parochial tendency is the greatest problem. The good news is the Ethiopian youth is determined to face tyranny by bringing its effort together, dispute lack of a national strategist, reinforcements and suppliers. This is really, really sad, but triumph and peace are closer.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule