• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስምና ገመድ!!

September 14, 2013 03:55 am by Editor 4 Comments

በተለያዩ ምክንያቶች ለረጅም ጊዜ አቋርጠነው የነበረውን የግጥም ጨዋታ እንደገና ጀምረናል፡፡ ከዚህ በፊት እናደርገው እንደነበረው አንባቢያን ይህንን ግጥም አንብባችሁ አስተያየታችሁን በግጥም እንድትሰጡና ጨዋታውን እንድታደምቁት እንጋብዛለን፡፡ ለዛሬ የመረጥነውን ግጥም ከነፎቶግራፉ ያገኘነው ከደመቀ ከበደ የፌስቡክ ገጽ ላይ ነው፡፡ገጣሚ ደመቀ ከበደን ለግጥሙና ለፎቶው ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡

ስምና ገመድ!!

አዝማሪ እንዲህ አለ፤
“ሰው ሰበበኛ ነው – ምክንያት አያጣም
እንኳን ዝናብ ዘንቦ – ሲዳምን አይወጣም፤”
እኔ ግን እላለሁ፤
አተተ በተተ
ወዘተ ወዘተ
በሚል አርቲ ቡርቲ – ዕድሜ ከምንጨርስ
ህይወት ከምናጣ
ፋይዳ ላለው ነገር – ቁልቁለት እንውረድ
አቀበት እንውጣ፤

ያኔ

አላስወርድ ካለህ – ወይም አላስወጣ
ማሰሪያ ከሆነህ – አሊያም ጋሬጣ
ያኔ አይንህን አውጣ
ወይ ሆ! ብለህ ውጣ፤

ያለዚያ

ቀብድ በበላች ሀገር – በድህነት ቁና
ሀብታምነት ከንቱ – ዝነኝነት መና፤
ነው እንጂ ነውና
በስም የሚከብሩ
በስም የሚከስሩ
በስም የሚወጡ
በስም የሚወርዱ
በስም የሚያለቅሱ
በስም የሚያብሱ
በስም የሚጥሉ
በስም የሚያነሱ
በሞላባት አገር – በስም ለታጠረች
ስምህ ገመድህ ነች
ድንገት ታስርሀለች – ወይም ታንቅሃለች፤
‹‹ከስብስም ይሸታል!›› – ብላ እየተረተች
ስምህ ሁሉን ሆና
ወይ ትጥልሃለች – ወይ ታነሳሃለች፤

ስለዚህ

በስም ከፍታ ላይ – እላይ እንድትወጣ
ጫፉን እንድትረግጥ
ዘዴ ዘይድና – ወይ ገመዱን ፍታ
ወይ ገመዱን ቁረጥ!!
(ደመቀ ከበደ – ጣና ዳር)

ከዚህ በፊት ያቀረብናቸው የግጥም ጨዋታዎች ላይ ትሳተፉ የነበራችሁ ሁሉ በድጋሚ እንድትሳተፉ፤ አዲሶችም እንዲሁ በጨዋታው እንድትገቡ ታድማችኋል፡፡ ምናልባት የበፊቶቹ ጨዋታዎች ምን ይመስሉ ነበር የሚለውን ለመመልከት ከዚህ በፊት ያቀረብናቸውን እንደሚከተለው አቅርበናል፡፡ ርዕሶቹ ላይ በመጫን ማንበብ ይቻላል፡፡

ሽ – ሽ – ት …! (አብዲ ሰኢድ)

በሳቅ ፍርስ አሉ (የካናዳው ከበደ)

ህልመኛው (ቃልኪዳን)

እኔ ምን አገባኝ? (ኑረዲን ዒሳ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው! says

    September 14, 2013 07:46 pm at 7:46 pm

    አውራ ድሮ!..ኪ ኪ..ኪ በለው! ኩኩሉ ቀረ ማለት ነው?
    ********************
    እናንት ምክንያተኞች ሰበብ ያሰራችሁ
    አትፈቱ አታስፈቱ ምነው ተተባተባችሁ ?

    ያኔ….
    “የዶሮ ልብ! ፈሪ!” ስትተርቱብኝ ኑሮ አስጠልቶኝ
    ይኼው ተመልከቱ የሠው ልብ እንዳለኝ
    ነፃነቴን መረጥኩ ገመድን አስፈታኝ
    ዘመን ተቀይሮ የሚገዛኝ የለ ኑሮ አስወደደኝ።

    አሁንማ..
    እርስ በእርስ ታስራችሁ በዝቶ ሰቆቃ ግፋችሁ
    ጠዋት ነቅቼ ንቁ !በቃ !ተነሱ !ብላችሁ
    ገና ሆ! ሳትሉ ደክሟችሁ ተኛችሁ ።

    ታዲያ…
    በመንቀሳቀስ መብቴ በእኔ ማፌዛችሁ ለነጻነት ስጠር
    ተናጋሪ እንስሳ ህዝብ ነኝ የሚል ሰው በቁሙ ሲታሠር
    እንዴት አይወደድ ዶሮ በሰው ሀገር?
    ************************
    የደመቀ ከባድ ነው በለው! ከሀገረ ካናዳ

    Reply
  2. emran says

    September 14, 2013 09:07 pm at 9:07 pm

    ስምን መገንባት ነው
    በጠንካራ አለት ላይ
    ኖሮ ለመታየት
    ከላይኞቹ ላይ
    ሞቶ ለመታወስ
    ከመቃብር በላይ

    Reply
  3. ወለላዬ says

    September 15, 2013 12:40 am at 12:40 am

    ከላይ ስመለከት መጀመሪያ ሳነብ
    መረዳት ችያለሁ ስው መውደዱን ሰበብ
    በዚሁ ጉዳይ ላይ ከሳፍኩት ግጥሞቼ
    እንካችሁ ላቅርባት አንዲቷን አውጥቼ

    “እጃችሁ ከገባ ድንገት ብታገኙት
    ሰይጣን ምናባቱ ደብድቡ ውገሩት
    ነገር ግን ጨርሶ አይገባም መግደል
    ጥፋት ስናተፋ ማን አሳተኝ እንበል”
    ግጥም ወለላዬ

    እውነት ነው በማለት ይሄን እንለፈው
    ውስት ገባ ብለን ሌላውን እንየው
    ሀብት ዝነኝነት መሞገስ መከበር
    ፍላጎቱም ቢሆን የሰው ልጅ ሲፈጠር
    ለፍቶ ብዙ ደክሞ ወይም እድል ቀንቶት
    ሁሉንም ጨብጦ ቢችልም ለማግኘት
    እስከመጨረሻው ስሙን አስከብሮ
    ካልያዘው በስተቀር ይገባል ከዜሮ
    ይሄ ነው ነገሩ ወንድሜ ደመቀ
    ለሁሉም አስረዳ ንገር ላላወቀ

    Reply
  4. YeKanadaw Kebede says

    September 17, 2013 12:31 am at 12:31 am

    አዎ…አንዱ እኔ ነኝ ሰበበኛው
    ስትጮሁ የማልሰማ፤ ስትነሱ የምተኛው
    ወሬ ስትጠርቁ
    ፀጉር ስትሰነጥቁ
    የዕምነት ገመዱ ሰለለ
    የስም ማዕረጉ ቀለለ
    ዓይናችን እያስተዋለ
    ክብራችን
    ታሪካችን
    ረከሰ…ጥምቡን-ጣለ
    ታዲያ
    ምን ቀረኝ ብየ ልውጣ
    የትኛው ቢሮ ልምጣ?
    ስትጮሁ የማልሰማ፤ ስትነሱ የምተኛው
    አዎ…አንዱ እኔ ነኝ ሰበበኛው

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule