• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመንጋ ፍትሕ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ መግለጫ

August 20, 2018 05:25 am by Editor Leave a Comment

የመንጋ ፖለቲካ እና የመንጋ ፍትሕ የትም ሃገር ሊከሰት የሚችል ነገር ነው። ተከስቶም ያውቃል።  የዘርፉ ባለሙያዎች ዋነኛ ምክንያቱ “በተቋማት እና በመንግሥት የተቆጣ ሕዝብ፣ ከምሬት እና ከቁጭት የተነሳ ለውጥ ፈላጊ ሕዝብ በሥሜት የሚወስደው በቀል አዘል “የፍትሕ ጥያቄ” ነው” ይሉታል።
በዚያ መልኩ ስንረዳው መፍትሔው ቀላል ይሆናል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመንጋ ፖለቲካውን እና የመንጋ ፍትሕን በዋነኛነት በሕዝብን ይሁኝታ (ለመልካም እሴት በመገዛት) እና የጸጥታ ኃይሉ በሚወስደው እርምጃ ብቻ ለመቆጣጠር ማሰባቸው ግን ሙሉ አይመስለኝም። 

ነፃነትል መሸከም አለመቻል አድርጎ መሳላቸውም አልተመቸኝም። ብዙ ትክክለኛ ጥያቄዎች “በመንጋው” ተነስተዋልና። ይልቁንስ ሕዝቡ በለውጡ ላይ ከፍተኛ ተስፋን በመጣሉ ዝቅተኛው ካድሬ እና የአስተዳደር አካል ሕዝቡ የሚፈልገውን ለማድረግ አለመቻሉ ነው። በዚህ ረገድም የፍትሕ ሥርዓቱ መሉ በሙሉ የፍትሕ ሥራን ሠርቶ ሕዝብን አገልግሏል ለማለት አያስደፍረም።

የመንጋ ፍትሕ ሌላ ምክንያቱ የዳሸቀ የፍትሕ አካላት ቅቡልነት እና ተዓማኒነት እንደሆነ ይገለፃል። (ሌላ ምክንያት ሊኖረው እንደሚችል ቢታወቅም)

ለረጅም አመታት የፖለቲካ ድርጅት ጠበቃ የነበረው የፍትሕ ዘርፉ አሁንም አንድም የተጠያቂነት አሠራርን ሳያሰፍን (ቢያንስ የፖለቲካ እስረኞችን ሙሉ በሙሉ ሳይፈታ፣ የማጎሪያ ቤት አሰቃይ የነበሩ ባለሥልጣናት ላይ ምንም ምርምራ ሳያደርግ) እንዴት ቅቡል እና ተዓማኒ ይሆናል፤ ሕዝቡስ እንዴት “የኔ ፍትሕ ሰጪ” ብሎ ይወሰደው?

Securitization and appealing to unbridled and unprincipled “forgiveness” will be inadequate. Appropriately recognizeing popular demand and making more delivery accordingly is a necessity. 

በሌላ በኩል የመንጋ ፍትሕ ተጨባጭ ምንክያት ዝቅተኛው ካድሬ አለመታደሱ (“አለመደመር”) ነው። ሙሰኛ ዞን እየቀተቀየረለት መሾሙ ነው። ከፍተኛው የሙስና አባቶችም “አለመደመር” ነው። ….…መደመር ማለቴ መቀነስ።

በሌላ በኩል ግን ጥሩ መልዕክት ነው…ሁለት ነጥቦችን ልጨምር.

፩. የጥንት የመልካም እሴቶች እና ሥነ መንግሥት እንደነበሩን ገልጸው ነበር። እጅግ በጣም ጥሩ ነው። ግን እነዚህ እሴቶች እና ሃገር በቀል የሆኑ የመንግሥት ሥርዓቶችን አንኮታኩተው ያደከሙት እና አንዴ ፊውዳል ሌላ ጊዜ ኮሚዩኒኒዝም፣ ሶሻሊዝም እና ካፒታሊዝም (ዴሞክራቲክ ዴቬሎፕመንታል ስቴት LOL) እያሉ ሀገሩን ወደ “STATE” ማሳደግ እንኳን ያቃታቸው ይዚሁ ሃገር ፖለቲከኞች ናቸው (ኢሕአዴግን ጨምሮ)።

፪. “አንድ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚንማኅበረሰብን መፍጠር” ያሉትን ሰማሁት። ይህ ሐረግ በሕገ መንግሥቱ መቅድም ላይ የሚገኝ ሲሆን ኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች የቡድን እና የግል መብት ተከብረውላቸው፣ የጋራ ጥቅም ተከብረውላቸው፣ ሠላም እና ዴሞክራሲ የሠፈነበት ሀገርን በጋራ መመሥረትን እንዲህ ብሎ ይገልፃል
” .….መጪው የጋራ ዕድላችን መመስረት ያለበት ከታሪካችን የወረስነውን የተዛባ ግንኙነት በማረምና የጋራ ጥቅማችንን በማሳደግ ላይ መሆኑን በመቀበል…. ”
የሕገ መንግሥት ባለሙያ ስላልሆንኩ ብዙም አስተያየት ባልችልም ግን ባለፉት 27 ዓመታት በዚህ ረገድ ምንል እንዳልተሠራ ለመናገር አሁን ያለንበት እርስበርስ ያለን ጥላቻ፣ መነቋቆር፣ መገዳደል ማየቱ በቂ ነው።

ምን ለማለት ፈልጌ ነው?

“አንድ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ”…ወይም በቀላሉ STATE ለመገንባት ብዙ ርቀት ይቀረናል…የጠቅላይ ሚኒስትሩም ትልቅ ፈተና እንደሚሆን አስባለሁ። 

Tactical Alliances (ካለ LOL)  ወደ strategic integration ይደጉ፤ እንትግሬሽንም አቃፊ ይሁን፣ ኢኮኖሚው ይነቃቃ፣ የሥራ ዕድል ይፈጠር፣ ያኔ መንጋ በሥራ ይጠመዳል (የፌስቡክ መንጋንም ጨምሮ)።
ግን ግን ቆይ የሕዝባዊ አመጹ ዋነኛ ጥያቄ ምን ነበር?

(እኔ ራሴው እንዳልረሳው ለማስታወስ ያህል ነው እንጅ እርስዎ “ጊዜ” ብለዋል)።

ከምንም በላይ ግን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሆይ  ኢሕአዴግን ማስተዳደር፣ መለወጥ ይቅናዎት። ካልሆነም እሱ ግትር ሆኖ አልቃና ብሎ ሲሰበር ኢትዮጵያን አደራ።

መንግሥቱ አሰፋ ነኝ

መልካም ቆይታ

(ፎቶ፤ የመንጋ ፍትሕ በታንዛኒያ ለማሳያ የቀረበ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule