• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምርጫ 97ና ትውስታዬ

May 21, 2014 12:09 am by Editor Leave a Comment

የምርጫ ነገር ሲታሰብ ሲነሣ በሁላችንም ልቡና የሚታሰበን ከፊታችን ድንቅ የሚልብን ምርጫ 97ዓ.ም. ነው፡፡ በምርጫ 97ቱ ወቅት መቸም የማይረሱን ጉልህ ጉልህ ጉዳዮች አሉ፡- ያ ምርጫ የወያኔ “ጠንካራ ተፎካካሪ ፓርቲ አላደለንም” የሚለው የምጸት ጸሎቱ ተሰምቶለት ተአምር ሊባል በሚችል መልኩ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከወያኔ የመቋቋም አቅም በላይ መልስ ያገኘበት፣ በዓለም ውስጥ ከታዩት ጥቂት ታላላቅ የሕዝብ ማዕበል ከታየባቸው ሰላማዊ ሰልፎች አንዱ የተደረገበት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከየትኛውም ሀገር ሕዝብ በላቀ መልኩ (ይሄንን ስል በድፍረት ነው) ያለውን የበሰለ ፖለቲካዊ (እምነተ-አሥተዳደራዊ) አስተሳሰብና አስደናቂ ሥነ-ሥርዓት (ዲሲፒሊን) ያሳየበት፣ የወያኔን ሲጀመር ጀምሮ ይዞት የነበረውን የውሸት የማስመሰል ዲሞክራሲ (በይነ ሕዝብ) ካባ አስወልቆ እርቃሉን በማስቀረት ትክክለኛ አንባገነናዊ ማንነቱት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ያጋለጠበት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደ አንድ ሀገር ሕዝብ ሁሉ ያለውን ጠንካራ አንድነት ያሳየበት፣ ተጨባጭ የኢትዮጵያ ተስፋ ለአፍታም ቢሆን የታየበት፣ በሕዝቡ ልቡና ውስጥ ሀገርን ከወደቀችበት ለማንሣት ያለውን የጋለ የተነቃቃ ስሜትና ቁርጠኛ ፍላጎት ያየንበት፣ ወዲያው ተመትቶ ወደቀ እንጅ የንባብ ባሕል የተቀጣጠለበት (እናቶች ሳይቀሩ ጋዜጣ ገዝተው “እባካቹህ አንብቡልኝ?” እስከማሰኘት የደረሰ)፣ ከረጅም ጊዜ ጨፍጋጋና ኃዘን የተሞላ ገጽታ በኋላ በሕዝቡ ገጽታ ላይ ተስፋን የሰነቀ የሞቀ ስሜትና ፈገግታ ደምቆ የታየበት ወዘተ.

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

እኔ ደግሞ በግሌ አንድ ልዩ ትዝታ አለኝ በዚያ አይረሴ የምርጫ ሂደት ውስጥ ጎልቶ ይታይ የነበረው በየ የምረጡኝ የምርጫ ቅስቀሳና የክርክር መድረኮች ላይ ይገለጽ የነበረው የየፓርቲው መሪ ቃል (slogan) ነበር፡፡ ከእነዚህ መሪ ቃሎች ውስጥ የቅንጅትና የኢሕአዴግ ተፎካካሪ ፓርቲዎች በዓለም አቀፍ የብዙኃን መገናኛዎች ሳይቀር ልዩነታቸውን በማንሣትም ጭምር ተደጋጋሚ ሽፋን ተሰጥቶት ነበር፡፡ እነዚህ መሪ ቃሎች የየፓርቲውን የብስለት፣ የአስተሳሰብ፣ የንቃተ ሕሊና ልዩነቶች አጉልተው ያሳዩ ነበሩ፡፡ የቅንጅትንና የኢሕአዴግን ብናይ የነበራቸው ልዩነት የኋላ ቀርና የዘመናዊ (የአናሎግና የዲጂታል) የዛሬና የነገ፣ የገጠርና የከተማ ያልሠለጠነና የሠለጠነ ያህል ዓይነት ነበር፡፡ የኢሕአዴግ የምርጫ ቅስቀሳ መሪቃል “ ንብን ይምረጡ! ንብ ታታሪ ሠራተኛ ናት፤ ንብ ማር ትሰጣለች ንብን ይምረጡ!” የሚል ነበር የቅንጅት ደግሞ “ ቅንጅትን አለመምረጥ መብት ነው፤ ግን የሀገርን የስቃይ የመከራ የችጋር የፈተና ዘመንን ማራዘም ነው ” የሚል ነበር፡፡ ይሄንን በሚገባ የተረዳው የኢትዮጵያ ሕዝብም በምርጫ ካርዱ ንቃቱን፣ ብስለቱን፣ ፍላጎቱን፣ ምኞቱን፣ ማንነቱን፣ አቋሙን ባረጋገጠ መልኩ ተናገረ ጮኸ አሰማ አስደመጠ፡፡ በሚያሳዝን መልኩ ወያኔም ይሁን የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በእሱ የንቃተ ሕሊናና የብስለት ደረጃ ያሉ ስላልነበሩ ምላሻቸው የሚያሳዝን ሆነ፡፡

“ቅንጅትን አለመምረጥ መብት ነው፤ ግን የሀገርን የስቃይ፣ የመከራ፣ የችጋር፣ የፈተና ዘመንን ማራዘም ነው” ይህ መሪ ቃል የእኔ ነበር፡፡

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule