• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦብነግ፤ ከህወሓቶች ጋር መቀመጥ በሕዝብ ደም መቀለድ ነው!

December 3, 2019 07:12 pm by Editor Leave a Comment

በቀን 10/03/2012 ዓ.ም ተፅፎ በቁጥር 07642/2019 ወጪ የተደረገው አስገራሚ ደብዳቤ ይድረስ “ለህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ፣ መቀሌ” በማለት ይጀምራል። ጉዳዩ፡- “ስለተጠራንበት ስብሰባ ይመለከታል” በማለት ይቀጥላል። የዚህን ደብዳቤ ትርጉምና ፋይዳ በቅጡ ለመረዳት የተፃፈበትን አውድ በአጭሩ መዳሰስ ያስፈልጋል።

በደብዳቤው ላይ ፊርማቸውን አኑረው የላኩት የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ-አውጪ ግንባር (ኦብነግ) ዋና ሊቀመንበር አቶ አብዲርሃማን መሃመድ ናቸው። ከላይ እንደተገለፀው ዋና ጉዳዩ ሰሞኑን በመቀሌ ከተማ እየተካሄደ ባለው ስብሰባ ላይ እንዲገኙ ከህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ለቀረበላቸው ጥሪ የተሰጠ ምላሽ ነው። ህወሓት በመቀሌው ስብሰባ ላይ እንዲገኙ ጥሪ ያቀረበላቸው በሥልጣን ዘመኑ በአሸባሪነት የፈረጃቸው የኦብነግ አመራሮች ናቸው።

እንግዲህ በአካባቢው ያለውን የተፈጥሮ ነዳጅ አውጥቶ ለመሸጥ ሲል የኦጋዴንን ህዝብ ከምድረገፅ ለማጥፋት ሲሰራ የነበረው፤ ለዚሁ ዓላማ አልሸባብ የተባለ ቡድንን ያደራጀው፣ በሶማሌላንድ በኩል የጦር መሣሪያ እያቀበለ በእጅ አዙር ሀገሩን ያስወረረው፣ የኢትዮጵያን ወታደሮችን ለሞት እየገበረ በፀረ-ሽብር ትግል ስም ከአሜሪካን እና እንግሊዝ ዶላር ሲቀበል፣ በሰላም አስከባሪ ስም ደግሞ ከተባበሩት መንግሥታት ይቀፍል የነበረው ህወሓት…። ከቻይና የነዳጅ አፈላላጊ ድርጅት ጋር በመሆን የተፈጥሮ ነዳጅ ለማውጣት በኦጋዴ ሕዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ የፈፀመው፣ አብዲ ኢሌ የሚባል ንክ ከኤሌክትሪክ ፖል ላይ አውርዶ የሶማሌ ክልል ፕረዜዳንት አድርጎ የሾመው፣ የሶማሌ ህዝብን ለአስራ አምስት አመታት ያህል በመከላከያ ሠራዊት እና በሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል እንደ ጠላት እያደነ ሲያስገድል የነበረው፤ ንፁሃንን ማሰርና መግደል በውስጡ ያለውን ሰይጣናዊ መንፈስ ማርካት ተስኖት እስር ቤት ውስጥ ጅብና ነብር አስሮ ሲያሰቃይ የነበረው፣… ያለ ምንም ሃፍረት፣ ፀፀት፣ ይቅርታ፣ ተጠያቂነት፣… በጠራው ስብሰባ መገኘት የሶማሌን ህዝብ ማዋረድ ነው። የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ-አውጪ ግንባር ከህወሓት ለቀረበለት የስብሰባ ጥሪ የሰጠው ምላሽ ይህንን መራራ ሃቅ እንዲህ ሲል ገልፆታል፡- 

ኦብነግ ከህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ለቀረበለት የስብሰባ ጥሪ በሰጠው ምላሽ ሊሰመርባቸው የሚገቡ ሦስት መሠረታዊ ነጥቦች አሉ። የመጀመሪያው ህወሓት ላለፉት 27 ዓመታት በሥልጣን ላይ በነበረበት ወቅት በንፁሃን ዜጎች ላይ ለፈጸመው ግፍና በደል ተጠያቂ ሊሆን ይገባል። ሁለተኛ በማንኛውም አግባብ ቢሆን ከህወሓት ጋር ትብብርና ጥምረት መፍጠር ላለፉት 27 ዓመታት ግፍና በደል በተፈፀመባቸው ዜጎች ደምና እምባ ላይ እንደመቀለድ ይቆጠራል። ሦስተኛ ከህወሓት ጋር በመተባበር የፌደራሊስቶች ግንባር ለመመሥረት በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙት ግለሰቦች እና ቡድኖች ህወሓቶች ቀድሞ በፈፀሙት እና ወደፊት በሚፈፀሙት የወንጀል ተግባር ላይ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ተሳታፊ እንደመሆናቸው መጠን ከተጠያቂነት አያመልጡም። (ኢትዮ ዊኪ ሊክስ፤ https://t.me/ethiowikileaks1)

ደብዳቤው እንዲህ ይላል፤

ተጨማሪ፤ በተያያዘ ዜና ህወሓት የፌዴራሊስት ግምባር ለመመሥረት መቀሌ ደፋ ቀና እያለ ባለበት ወቅት ከጋበዛቸው ፓርቲዎችና ቡድኖች ግማሽ ያህሉ ብቻ የተገኙ ሲሆን አንጋፋዎቹና ተስፋ የተጣለባቸው ኦፌኮ፣ ኦነግ፣ … አልተገኙም፤ ኦብነግ አለመገኘት ብቻ ሳይሆን ከዚያ ይልቅ “የምንፈልጋት ኢትዮጵያ በ2032” በሚል ርዕስ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ባለው ሀገር አቀፍ የውይይት መድረክ ላይ ተገኘቷል።  

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ህወሓት በኦጋዴን ወገኖቻችን ላይ የፈጸመውን ግፍ አስመልክቶ ከዚህ በፊት “ኦጋዴን፤ የኢትዮጵያ [የህወሃት] ድብቅ ኃፍረት”፤ “አንዳችሁንም አናስተርፍም፤ እንጨርሳችኋልን” የህወሃት ነፍጠኞች – በሚል ርዕስ ዘገባ አውጥቶ ነበር። ነውር ጌጡ፤ ውርደት ቀለቡ የሆነው ህወሓት ይህንን ግፍ የት አስቀምጦ ይሆን “አሸባሪ” እያለ ሲጠራው የነበረውን ኦብነግ ለስብሰባ የጠራው? ሙሉ ዘገባውን እዚህ ላይ ማንበብ ይቻላል።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: federalist meeting, Left Column, onlf, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule