• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የወንድሞቻችን ቅኝ ተገዥዎች አንሁን

January 31, 2016 07:06 am by Editor Leave a Comment

ዛሬ ታላላቅ አፍሪካውያን ከተናገሩት መነሳትን መረጥሁ። አንጋፋው ደቡብ አፍሪካዊ ታጋይ ዴዝሞን ቱቱ “When the missionaries came to Africa, they had the Bible and we had the land. They said ‘Let us pray’. We closed our eyes. When we opened them we had the Bible and they had the land”. ተቀራራቢ ትርጉሙ “ሚሲዮናውያን ወደ አፍሪካ ሲመጡ መጽሃፍ ቅዱስ ይዘው ነው። እኛ ደግሞ መሬት ነበረን። ‘እንጸልይ’ አሉን። ለጸሎት ዐይናችንን ጨፈንን። ጸሎቱን ጨርሰን ዐይናችንን ስንከፍት ግን እኛ መጽሃፍ ቅዱስ ብቻ ታቅፈን ስንቀር እነሱ ግን መሪታችንን ይዘውት አገኘን” የሚል ነው።

አዎ! ደቡብ አፍሪካ፣ ኬንያ፣ ኡጋንዳ፣ ዚምባዌ ወዘተ… በቅኝ ግዛትነት ለመውረር የመጡት ነጭ ሚስዮናውያን ቀጥሎም መሳርያ የታጠቁ ናቸው። ከነጮች ወረራ ራሷን ተከላክላ የኖረችውን ኢትዮጵያን ባለፈው ሃያ አምስት ዓመት የወረሯት የእኛ መልክና ደም ያላቸው ወንድሞቻችን ወያኔዎች አገሪቷን ሲቆጣጠሩ አንገታቸው ላይ ኩሺት (መቀበርያ ጨርቅ) ምላሳቸው ላይ የዘረኝነት ከፋፋይ መርዝ ይዘው መጡ። “ሁላችንም በጎሳ እንደራጅ፣ በማንነታችንና በቋንቋችን እናተኩር” ብለው ሰበኩን።

በተቀነበበልን የጎጥ አጥር ገባንላቸው፤ ያለፈና አስከፊ የሆነውን ታሪካችንን እየመረጥን አፅም ቆፈርን፤ የምንበቃቀልበትን ስልት እያዘጋጁ ሲሰጡን ተቀበልን። ካለፈ ስህተት የባሰ ስህተት ውስጥ ገብተን መሳርያቸው ሆንን። አሁን ከእንቅልፋችን ባንነን ዐይናችንን ስንገልጥና ልቦናችንን ስናቀና መሬታችን፣ ቀሪው ሃብታችን፣ አጠቃላዩ ህልውናችን በእጃቸው ውስጥ ሆኖ ሲሳሳቁና ሲዘባበቱብን አገኘናቸው። እኛ እጅ የቀረው ለብሄር ብሄረሰብ መብታችን መከበር ራቁታችንን በየዓመቱ መጨፈርና በርሃብ፣ በስደት፣ በአጋዚ ጥይት ማለቅ ሆነ።

አባቶቻችን መጽሃፍ ቅዱስ ይቅርና መድፍ ይዘው የመጡ የውጭ ጠላቶችን እጃቸውን እየሰበሩ መልሰዋቸዋል። እኛ ልጆቻቸው ግን የኤይድስ ቫይረስ የሰውነት ሴሎችን ተመሳስሎ በማጥቃቱ መከላከል እንደሚያስቸግር ሁሉ የእኛን ደም፣ ቀለምና ቋንቋ የተካኑ የባንዳ ልጆችን ለይቶ ማጥቃት ስላልቻልን ለዚህ ወርደትና ውድቀት በቃን።

የህወሃቶች ብቸኛው መሳርያቸው ህዝብን መለያየትና መከፋፈል ነውና ይህንን ብቸኛ መርዛቸውን መቋቋም ከቻልን ሰላማዊ አገር የመገንባት ተስፋችን እውን መሆኑ የማይቀር ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ዐይኑን መግለጥ የጀመረው ኢትዮጵያዊ የተከሰተለት እውነት ቢኖር ይኼው ነው።

አንገታቸው ላይ ኩሺት ብቻ ጠቅልለው የመጡት ወያኔዎች በአንድ ጀንበር ሚሊዮነር፣ የባለብዙ ፎቅ ጌታ፣ የከተማና የእርሻ መሬት ባለቤት፣ በውጭ አገራት የብዙ ካምፓኒዎች ባለድርሻ ሲሆኑ፤ ቀሪው ኢትዮጵያዊ የከተማ መሬቱን ተነጥቆ ዘበኛቸው፣ ከእርሻውን ተፈናቅሎ የቀን ሠራተኛቸው፣ መብራቱን ተቀምቶ ሻማ ይዞ የሚያበላቸው ተደርጓል። ይህ ሁሉ ካስከፋውና ተስፋ ከቆረጠ ደግሞ በስደት የየአገሩ እስር ቤት ታዳሚና ኩላሊት ገባሪነት ይጠብቀዋል።

ዛሬ የወላጆቻቸውን መሬት አይነጠቅም ብለው የተነሱ የኦሮምያ፣ የጎንደር፣ የጋምቤላ፣ ልጆችን የሚጨፈጭፉ ወያኔዎች አገዛዛቸውን ዘለዓለማዊ ለማድረግ የትምህርት ሥርዓቱን ሲገድሉ የእነሱ ልጆች በስዩም መስፍን የበላይ ተቆጣጣሪነት ልጆቻቸው በቻይናና በምዕራቡ ዓለም ትልልቅ ዩኒቨርስቲዎች ተምረው አሁን ያሉትንና ወደፊትም የሚፈጠሩትን የህወሃት ካምፓኒዎች እንዲመሩ፤ እያረጁ ከፖለቲካው የሚገለሉ አባቶቻቸውን የሚተኩ መሳፍንት እንዲሆኑ እየተዘጋጁ ነው። አገር ውስጥም የመለስተኛ ህወሃት ልጆች አማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ ሶማልኛ፣ ሲዳምኛ፣ ጉራጌኛ ወዘተ … እንዲሰለጥኑ ተመቻችቶላቸው በመላ አገሪቱ እንዲሰማሩ ሲደረጉ ሌላው ህዝብ ከራሱ ቋንቋ ውጭ ሌላውን በጥላቻ እንዲያይና ወንዝ በማያሻግር ሁኔታ በመንደሩ ታውሮ እንዲኖር ፈርደውበታል።

ወያኔዎች ይህ አስማታቸው አሁን የያዘላቸው አይመስልም። ዓላማቸው የገባው ኢትዮጵያዊ ከዳር ዳር ተንቀሳቅሷል። ዐይኑን ገልጧል። እየቆየም አጥርቶ ያያል። በተለይም ሁለቱን ታላላቅ ህዝብ ማለትም አማራውንና ኦሮሞውን ለመለያየት ብዙ የደከሙበት ቢሆንም አሁን ህዝቡ የአንድነትን መንገድ በመምረጥ ላይ ነው። ላለፉት ሰላሳ አመታት የተፈጠረው የልዩነት ክፍተት ቀላል ባለመሆኑ የብዙ ቅን ኢትዮጵያውያንን ድካም የሚጠይቅ ሥራ ገና ከፊታችን አለ።

እንደ ህወሃቶች የእንግሊዞች መርዝ ያንገበገባቸው የኬንያውያን የነፃነት አባት ጆሞ ኬንያታ ለወገኖቻቸው የሰጡት ምክር የቆየ ቢሆንም በተመሳሳይ ሁኔታ ላለነው ኢትዮጵያውያን ይጠቅማልና እንዲህ ላቅርበው። “የነበረው የዘር ጥላቻ ማብቃት አለበት። የጎሳ ጥቃትም ሊቆም ይገባል። ባሳለፍነው መራራ ሁኔታ ውስጥ አንኑርበት። ካለፉት የከፉ ታሪኮቻችን ይልቅ የወደፊቷን አዲሷን ኬንያ ማለም እመርጣለሁ። ይህንን ዓይነት ብሄራዊ ስሜትና ማንነት ከፈጠርን የኤኮኖሚ ችግራችንን ለመፍታት ረጅሙን ጉዞ መሄድ እንችላለን” ብለዋል። እኛም ብንሆን ያለፉ አስከፊ ታሪኮቻችንን እያስታወስን ወደ ኋላ ከምንድህ የወደፊቷን የጋራ ኢትዮጵያ እያለምን ወደ ፊት ብንራመድ ይጠቅመናል።

አዎ! ባለፉት ጊዚያት አባቶቻችን ሉአላዊነታችንን ለማስጠበቅ የከፈሉትን ጉልህ አኩሪ መስዋዕት ያህል ብዙ አስከፊና አሳፋሪ ታሪክ አለን። ያንን የሚክዱትም ሆኑ ያንን እየመረጡ የሚቆፍሩና በትናንት የሚኖሩ ዛሬን የማያዩ ጨለምተኞች ናቸው። ከሁሉም በላይ የወያኔ ጥሩ መሳርያዎች ይሆናሉና። የኢትዮጵያ አፈር ትናንት በደርቡሾች፣ በግብፆች፣ በጣልያኖች ጥይት ተደራርበው ከወደቁ ኦሮሞዎች፣ አማሮች፣ ትግሬዎች፣ ወላይታዎች፣ ሶማሌዎች፣ ሲዳማዎች ወዘተ ደምና አጥንት ውህደት የተቀመመ ነው። ዛሬም በወያኔ የአጋዚ ጥይትና ዱላ በኦጋዴን፣ በጋምቤላ፣ በአዲስ አበባ፣ በአምቦ፣ በወለጋ፣ በሃረር፣ በጎንደር በሚወድቁ ወጣቶች እየታደሰ ያለ አፈር ነው የኢትዮጵያ አፈር።

ወያኔ ለሱዳን “እንካ” ብሎ ቆርሶ የሚሰጠው ዳቦ አይደለም የኢትዮጵያ መሬት። የአፄ ዮሃንስና ከሁሉም ጎሳ የተውጣጡ ኢትዮጵያውያን አፅም የተቀበረበትን መሬት ነው የጣልያን እንቁላል አቅራቢ ሹምባሽ ልጆች ለማስረከብ በጓዳ የሚስማሙት። የአብዲሳ አጋ፣ የአበበ አረጋይ፣ የበላይ ዘለቀ፣ የገረሱ ዱኪ፣ የአሞራው ውብነህ፣ የአሉላ አባነጋ፣ የጀጋማ ኬሎ፣ የባልቻ አባነፍሶ አገር እንዲህ በቀላሉ ለባዕድ ስትሸጥ ልጆቿ በዝምታ ልንመለከት አይገባም።

ሚሊዮኖች በርሃብ እየረገፉ፣ ሺዎች እየተሰደዱ፣ ሺዎች በእስር እየማቀቁ፣ ሚሊዮኖች የሃፍረት ማቅ ለብሰው በሚኖሩባት፤ ጥቂት ዘረኞች አቅል ባጡባት አገር ላይ ዛሬ እየኖርን ትናንትን ለልዩነታችንና ለድክመታችን ምክንያት ማድረጉን እናቁም። ከዛሬው ተጨባጭ ችግራችን ተነስተን የነገዋን የሁላችን የጋራ አገር የመገንባት ተልዕኮ ላይ እናተኩር። ለነገ ተስፋችን እንቅፋት የሆኑ ጥቂት ዘረኞችን እንታገል። ከራሳችን ወንድሞች ቅኝ አገዛዝ ስር ነፃ እንውጣና ኢትዮጵያንና ህዝቧን ነፃ እናውጣ!

amerid2000@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule