• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አቶ ለማ መገርሳ – በህወሃት የማስፈራሪያ አጣብቂኝ ውስጥ

January 10, 2020 01:03 am by Editor 3 Comments

ከለውጡ ሾፌሮች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ለማ መገርሳ የሽግግሩ ጊዜ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆኑ ጃዋር መሐመድ አጥብቆ ሲከራረከር ነበር። አቶ ለማ የፌዴራል ፓርላማ ተወካይ ባለመሆናቸው እርሳቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር እንዳይሆኑ የሚከለክላቸው መሆኑ የታወቀ ቢሆንም በወቅቱ ግን ጃዋር ከጓደኞቹ እነ ሕዝቅኤል ገቢሣ ጋር በመሆን “ኢህአዴግ አዲስ መመሪያ/ሕግ አውጥቶም ቢሆ አቶ ለማ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊያደርጋቸው ይገባል” በማለት ሃሳብና መመሪያ ቢጤም ሲሰጥ ነበር።

ጃዋር ያለውና ያሰበው ሳይሆን አቶ ለማ በለውጡ ሙቀት ውስጥ ባሉበት ወቅት “እኔና ዐቢይን ሞት ብቻ ነው የሚለየን” በማለት የድርጅት ሊቀመንበርነታቸውን ለዶ/ር አብይ አሳልፈው በመስጠት ዐቢይ አህመድ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆን የበኩላቸውንና ድርጅታዊ ኃላፊነታቸውን ከባልደረቦቻቸው ጋር ሆነው እውን አደረጉ።

የሆሮ ጉድሩ ተወላጅ የሆኑት አቶ ለማ በዚህ ተግባራቸውና ከለውጡ መፈንዳት ጀምሮ ለህዝብ ባቀረቡት ዲስኩር የተወደዱትን ያህል ከህወሃት አፍቃሪዎችና ጭፍራዎች ዘንድ ግን ተቃውሞ በስፋት ይሰነዘርባቸው የጀመረው ወዲያው ነበር። በተለይም በኦሮሚያ የደኅንነት ቢሮ ሥልጣናቸው ወቅት የሰሩትን በመጥቀስ። 

ስለ አዲስ አበባ የሕዝብ አሠፋፈር (ዴሞግራፊ) የተናገሩት ቅጂ አደባባይ ከወጣ በኋላ ተቃውሞ እየከበባቸው የመጣው አቶ ለማ በዛው ቅጽበት ከጃዋር መሀመድ ጋር በየዕለቱ እንደሚገናኙና አብረው እንደሚሰሩ ከየአቅጣጫው መረጃዎች ይሰራጩ ጀመር። በዚያው መጠን ከዶ/ር ዐቢይ ጋር ልዩነት እንደፈጠሩ በተደጋጋሚ በተለያዩ የሚዲያ ማሰራጫዎችና ማህበራዊ ገጾች ተዘገበ። በዳያስፖራ የሚገኙትና ራሳቸውን ተንታኝ አድርገው የሰየሙ ዜናውን ዞሩበት። 

ከኦሮሚያ ርዕስመስተዳድርነታቸው ተነስተው ወደ መከላከያ ሚኒስትርነት የመዛወራቸው ሚስጢርም ይኸው የልዩነቱ ነጸብራቅ እንደሆነ ትርጉምና ትንታኔ እየቀረበበት ከሚዲያ ወደ ሚዲያ ተራባ። በመጨረሻም ራሳቸው አቶ ለማ በቪኦኤ ቀርበው ልዩነት እንዳላቸውና “እንደመር” እያሉ ሲፈክሩበት ከነበረው ሃሳብ ጋር መጣላታቸውን ይፋ አደረጉ።

በተለይም የብልጽግናን መመሥረት፣ የኢህአዴግ እህት ድርጅቶችና አጋር ድርጅቶች ውህደት እንደማይቀበሉ ሲናገሩ ተቃውሟቸውን በሚያሳምን መንገድ ባለማስረዳታቸው ሕዝብ ደነገጠ። መሠረታዊ ምክንያታቸው ምን ይሆን ሲል በማኅበራዊ ሚዲያ ክርክርና መላምት ማስቀመጥ ተጀመረ። 

የለውጡ ተጻራሪዎችና ጭፍን ነቃፊዎች፣ በተለይም የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር በፓርቲ ደረጃ፣ እንዲሁም ደጋፊ የማኅበራዊ ገጽ ጭፍሮቹ የአቶ ለማን ቃለ ምልልስ አጯጯሁት። “ብለን ነበር” ሲሉ የለውጡ ሃዲድ እንደተሰበረ፤ ባቡሩ አቅጣጫውን እንደሳተ አወጁ። 

የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ከዘወትር ታማኝ ምንጮቹ ባገኘው መረጃ አቶ ለማ እዚህ ችግር ውስጥ የወደቁት ፈልገውና ወደው እንዲሁም የለውጡ የትግል አጋሮቻቸውን ለማስቀየም አስበው ሳይሆን ከፌደራሉ የመረጃና የደህንነት አጄንሲ (ደኅንነት) ጋር በጥምረት በሚሠራው የኦሮሚያ የስለላ መዋቅር ውስጥ በከፋ ሁኔታ ተነክረው ስለነበር ነው።

“ማበስበስ” በሚባለው በህወሃት ስልት ውስጥ በኦሮሞ ተወላጅ የኦነግ ታጋዮች፣ ደጋፊዎችና ተቃዋሚዎች ላይ ሲያከናውኑት የነበረው የስለላ ሪፖርት ሪኮርዶች ህወሃት እጅ አሉ። ህወሃት በክልሉ መሪ ሳይቀር “ሚስጢር እናወጣለን” በሚል የሚሰነዝሩት ዛቻ በአብዛኛው በአቶ ለማ ላይ ያነጣጠረ መሆኑንን የጎልጉል ዘጋቢ ለህወሃት ቅርብ የሆኑ ክፍሎችን ጠቅሶ ዘግቧል። ይህ የህወሃት ዛቻ በዶ/ር ዐቢይ ላይ ቢሆን ኖሮ መዛትም አያስፈልጋቸውም ነበር፤ ውሸት ፈጥሮ በሚያናፍሰው የዲጂታል ወያኔ መስተጋብራቸው ያለገደብ ያራግቡት ነበር።  

ከወራት በፊት “አቶ ለማ የኦሮሞ ተወላጆችን ሲያሳድድ የነበረ ዋናው ወንጀለኛ ነው” ሲል የህወሃት ደጋፊና ፕሮፓጋንዲስት የሆነው ዳንኤል ብርሃኔ፤ ጌታቸው አሰፋ ላይ የሚቀርበውን የነፍሰ በላነት ውንጀላ ለመከላከል ባቀረበው ጽሁፍ ላይ መጥቀሱ አይዘነጋም። ከዚያም በኋላ የብልጽግና ፓርቲ መቋቋሙን ተከትሎ ይኸው ሚስጢር ይፋ እናደርጋለን የሚለው ጉዳይ በስፋት ሲናፈስ የከረመውም ያለምክንያት አልነበረም።

በዚሁ ምክንያት አቶ ለማ ከኦሮሞ ህዝብ ሊነጥላቸው የሚችለው ይህ ሚስጢር እንዳይወጣ ኦዲፒን ወይም ብልጽግና ፓርቲን እንዲለዩና ህወሃት ጠፍጥፎ እየሠራቸው ካሉት የፌዴራል ኃይሎች ጋር እንዲዋሃዱ አማራጭ እንደቀረበላቸው ነው ለህወሃት ቅርብ የሆኑት ለጎልጉል መረጃ የሰጡት።

ህወሃት ከፌዴራል ኃይሎች ጋር በማበር ዳግም መንግሥት ለመሆን እንደሚሰራ በግልጽ ማሳወቁና አቶ ለማም ፓርቲያቸውን ጥለው ወደ ፌዴራል ኃይሎች የመንደርደራቸው ዜና ሌላ ምክንያት እንደሌለው የጎልጉል ዘጋቢ ካሰባሰበው መረጃ ለመረዳት ተችሏል።

አቶ ለማ መገርሳ ብልጽግና መቃወምና መደመርን በማጣጣል የተናገሩትን ቃለ ምልልስ “አንዱ የመጫወቻ ካርዴ ነው” ሲል ገልጾት የነበረው ጃዋር ረቡዕ ዕለት ለኤልቲቪ ባልደረባ ጋር ባደረገው ጭውውት መሳይ ቃለ መጠይቅ፣ በመጪው ምርጫ አቶ ለማን አካትተው ወደ ውድድር እንደሚገቡ በገደማዳሜና በሳቅ አረጋግጧል። ጃዋር ለጊዜው መናገር ያልፈለገው የፓርቲዎች ጥምረት እንደሚኖርም ጠቁሟል። ህወሃትም በጌታቸው ረዳ አማካይነት ጃዋር ከተቀላቀለው ኦፌኮ ጋር ህወሃት ግንባር የመፍጠር ሥራ እየሠራ መሆኑንን የበቀለ ገርባን ስም በመጥራት አረጋግጧል። ይህ ሁሉ ትሥሥርና ቅንነት የጎደለው፣ በሤራ የተሸበበ “ሥልጣን ወይም ሞት” በማለት በጭፍን የሚመራው ፖለቲካ አምስት ሺህ ሰው የተገበረበት ህወሃትን የማስወገድ ትግል ወዴት ይወስደዋል? ወይም ወዴት ይመልሰዋል? የሚለው ጥያቄ በስፋት እንዲነሳ ያደርገዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, jawar massacre, lemma megerssa, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Wondemagne Ejigu says

    January 10, 2020 02:19 pm at 2:19 pm

    አብይና ለማ በሕወሐት ጊዜ በአገዛዙ የስለላ መዋቅር ይሰሩ እንደነበር የሚታወቅ ነው። ሕዝቡም ይሕን እያወቀ ነበር እኮ ለውጡን በይቅርታ መንፈስ ሙሉ ለሙሉ የደገፈው። በእርግጥ የለማ አስተዋጽኦ የከፋ ቢሆንም። ነገር ግን አሁን ላይ ቆመን አቶ ለማን ሕወሐት የበፊት ታሪክ መዛ ስላስፈራራች ነው፣ አቋም የለወጡት-የሚለው ክርክር ውሐ አይቋጥርም። ቢያንስ፣ቢያንስ በቃኝ ብለው ስልጣናቸውን በመልቀቅ ሕዝብ የሰጣቸውን ክብር መጠበቅ ይችሉ ነበር።የአሁኑ እርምጃቸው በጥፋት ላይ ሌላ ጥፋት ከመደራረብ ያለፈ ፋይዳ የለውም!

    Reply
  2. nahom asnake says

    January 10, 2020 06:56 pm at 6:56 pm

    You hateful idiot!! You will lose.

    Reply
    • Wondemagne Ejigu says

      January 11, 2020 12:53 pm at 12:53 pm

      Lose what? If I may ask the smart Nahom

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule