• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መሬት ላራሹ! Land tenure!

February 6, 2019 09:54 am by Editor 1 Comment

የኢትዮጵያን የክልሎች ወሰን ጥያቄ የሚፈታው የመሬት ላራሹ ጥያቄ ሲመለስ ነው። የኢትዮጵያ ህገ-መግስት አንቀጽ 40 ንኡስ አንቀጽ 6 ላይ ሲናገር “የኢትዮጵያ መሬት ባለቤትነት የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች…” ይላል። ይህ ማለት የሃገሪቱ መሬት በብሄሮች የተያዘ የቡድን ሃብት ነው ማለት ነው።

የደርጉ መንግስት መሬትን ከከበርቴው ነጥቆ ለመንግስት ያደረገ ሲሆን ይሄኛው መንግስት ደግሞ  ለቡድኖች ኣድሏል። እነዚህ ሁለት የመሬት ሃብት ዝውውሮች ችግሮች ኣሉባቸው። መሬት ላራሹ ማለት መሬት ለሚሰራበት ኢትዮጵያዊ ሁሉ ወይም ለዜጋው ከነ ሙሉ መብቱ ይሰጥ የሚል እንድምታ ነው ያለው። ይህንን ጥያቄ መመለስና የመሬትን የሃብት ዝውውር ከቡድን ወደ ግለሰብ በማዛወር የወሰን ጥያቄዎችን እስከ ሃቹ መፍታት ይቻላል። ይህ የተቋቋመው የማንነት ኣስተዳደርና ወሰን ኮሚሽን ይህንን ኣሳብ እንዲያየው እጠቁማለሁ።

በቡድን የተያዘው መሬት ወደ ግል ሲዞር የብሄሮች የወሰን ጥያቄ አለቀለት ማለት ነው። ስለዚህ ኮሚሽኑ በክልሎች መካከል መስመሩ የት ጋር ይሁን? ብሎ ከማሰብ ከአሁኑ መሰረታዊ የሆነ የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ እንዲፈታ መንግስትን ማሳሰብ ኣለበት። መሬት ላራሹ ከሆነ ኢትዮጵያውያን በወሰን አይጋጩም። መሬት የግል ይሁን ሲባል አንዳንድ ኮሙዩኒቲዎች መሬት ኣያስፈልጋቸውም ማለት ኣይደለም። መሬትን ከብሄር ባለቤትነት አውጥቶ ነገር ግን አንዳንድ ኮሙዩኒቲዎች ደግሞ የመሬት ባለቤት እንዲሆነ ማድረግ ይቻላል። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ የመሬት ፖሊሲዋን በሚመለከት የሚከተለውን ለውጥ ብታደርግ ብዙ እቆቅልሶቿ ይፈታሉ።

  1. መሬትን የግል በማድረግ (Privatization)
  2. ኣንዳንድ የግጦሽ ቦታውችን የአምልኮ ስፍራዎችንና የባህል መከወኛ ስፍራዎችን በቡድን እንዲያዙ ማድረግ
  3. ወንዞችን ተራሮችን ሰው ያልደረሰባቸውን ቦታዎች መንግስት እንዲይዝ ማድረግ ይገባል።

ይህ የመሬት ፖሊሲ በተለይ የወሰን ጥያቄን ግሩም ኣድርጎ ይፈታል። የማንነትና የአስተዳደር ጉዳዮችን ደግሞ በሁለትዮሽ የፌደራል ስቴት (two federal states) ግንባታ መመለስ ይቻላልና ኮሚሽኑም መንግስትም የለውጡ ሃይልም ይህንን ኣሳብ እንዲያስበው እንመክራለን።

ሁለትዮሽ የፌደራል ስቴት  ማለት በአንድ በኩል የብሄር ባህላዊ የፌደራል ስቴትና በሌላ በኩል ሲቪክ የፌደራል ስቴት ወይም የዜጎች የፌደራል ስቴት በመመስረት የማንነትና ኣስተዳደር ጉዳዮችን ማስታረቅ ይቻላል። ይህ መንገድ እጅግ ኣስፈላጊ ነውና ኮሚሽኑ ይህንን ከግንዛቤ እንዲያስገባ ከወዲሁ እጠይቃለሁ። የሁለትዮሽ የፌደራል ስቴት ግንባታው በሁለት ጽንፍ ያለውን ፖለቲካ በዶክተር አብይ አህመድ አገላለጽ “ዋልታ ረገጥ” ፖለቲካችንን ያስታርቃል። የዜግነት ፖለቲካንና የቡድን መብትን አቻችሎ ይይዛል።

ከፍ ሲል እንዳልኩት የመሬት ላራሹ ጥያቄ ከተመለስና ከላይ ባነሳሁት መሰረት መልክ የመሬት ይዞታ ፖሊሲው ከተቀረጸ የአዲስ ኣበባ ጥያቄም ይፈታል። የመሬት ላራሹ ጥያቄ የከተማ ቦታንም ይመለከታልና ከተሜው የቦታው ባለቤት ሲሆን የአዲስ ኣበባ የባለቤትነት ጥያቄ እስከ ሃቹ ተፈታ ማለት ነው። የመሬት ፖሊሲያችን ሲፈታ መሬት ላራሹ ሲሆን ደቡብ ውስጥ ያሉ የወሰን ግጭቶች መፈናቀሎች ሁሉ ይቆማሉ። ስለዚህ ዛሬም መሬት ላራሹ! ዛሬም መሬት ላራሹ! ዛሬም መሬት ላራሹ! … ወጣቶች ይህንን ጥያቄ አንግበው የቀዳሚውን ትውልድ ጥያቄ ሊቋጩት ይገባል። አዲስ ኣበቤዎች ይህንን ጥያቄ ሊያነሱ ይገባል። ገበሬው ይህንን ጥያቄ ሊያነሳ ይገባል።

የዶክተር ኣብይ መንግስት ወደ ለውጥ ሲገባ ከሚመለከታቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል ይህ የመሬት ፖሊሲና የማንነት ጉዳዮች ናቸው። ማንነትን ከፍ ሲል እንዳልኩት በሁለትዮሽ ፌደራል ስቴት ቤቶች ጠብቆ የወሰኑን ጉዳይ በመሬት ፖሊሲ ለውጥ እስከ ሃቹ መዝጋት ይቻላል። መሬት ላራሹን የማይደግፍ ኦሮሞ፣ ኣማራ፣ ትግሬ፣ ወላይታ፣ ጉራጌ፣ ወዘተ ኣለ ብየ ኣላምንም። የዜጎች የመሬት ሃብት ባለቤትነት (land ownership) ሲመለስ ልማት ይፈጥናል እንዳልኩት የወሰን ጉዳይ ያልቅለታል። እናም መሬት ላራሹ!

geletawzeleke@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: land, Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. gi Haile says

    February 8, 2019 05:01 pm at 5:01 pm

    ብዙዎች የሞቱለት የመሬት ለኣራሹ ጥያቄ ዛሬም ኣልተሠለሰም። ይህ ከ 40 አመት በላይ ደም ሲያፋስስ የቆየው የመሬት ጥያቄ በወቅቱ ካልተፈታ በ27 አመት መፍትሔ አድርጎ ሕወኣት ያወጣው የድንበርና የመሬት ፖሊስ ጨርሶ ደርግ አድርጎት ከነበረው የከፋ ፖሊስ ነበር። የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥያቄው ከመጀመሪያው ዲሞክራሲ፣ መሬት ለኣራሽ፣ የዜጎች እኩልነት መብት ጥያቄ እስከዛሬ መልስ ያላገኘ መመለስ ያለበት መሠረታዊ ጥያቄ ነው። የጊዜውም ጥያቄ ሰለሆነ መልስ ሊሰጠው የሚገባ ነው። ድልና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ለኢትዮጵያ ሕዝብ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule