• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ካሚል ሸምሱ እውነት ነጻ ያወጣችው ጀግና

September 20, 2016 11:35 pm by Editor Leave a Comment

እውነትን መናገር ለራስ ነው የሚያምኑበትን ሳይናገሩ ከመኖር ይሰውረን!!!

ከአንድ አመት በፊት ልክ በዛሬዋ እለት ስለ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ የማውቀውን ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ እስከ ቂሊንጦ በሚል ርእስ አንዲት ጽሁፍ ጀባ ብዬ ነበር፤ ዛሬ ደግሞ እነ ካሚል ሸምሱ ከቂሊንጦ ቃሊቲ ከዛም ወደ ቤተሰብ ተቀላቅለዋል፤ ደስ የሚያሰኝ ዜና ነው፡፡

በርካታ ጓደኞቼን ስለ ካሚል ሳጫውታቸው በቅድሚያ ግራና ቀኛቸውን ይመለታሉ፣ ይቀጥሉና አንገታቸውን እስቲሰበር ድረስ ወደ ኋላቸው ገልመጥ ይላሉ፣ ይቀጥሉና የአግአዚ ስናይፐር እንዳይመታቸው ይመስል ወይንም ነፍሴን አደራ በሰማይ በሚመስል መልኩ ሽቅብ ያንጋጥጣሉ፣ በመጨረሻም ራሴውኑ በጥርጣሬ አይን ይመለከቱና ስለ ካሚል ሸምሱ ያላቸውን አስተያየት በሹክሹክታ ይነግሩኛል፡፡

ብሽቅ ብዬ ትቻቸው ልሄድ ስልም ምክንያታቸውን ይገልጹልኛል፣ ‹ምን ነካህ አብረውን የተማሩት እነ እከሌ እከሊት እኮ የማእከላዊ ባልደረባ ሆነዋል፣ እነ እንትና እኮ የደህንነቱን መስሪያ ቤት ከሚያሾሩት ውስጥ ይመደባሉ፣ በዛ ላይ ደግሞ ባለትዳርና የልጆች አባት ነኝ› ሲሉ ይደመጣሉ፤ እንዲህ አካባቢያቸውን በአይነ ቁራኛነት ሲከታተሉ ሳይ አዝኜላቸዋለው፤ በአንጻሩ ደግሞ ለመብቱ መከበር ሲል ዋጋ የከፈለውንና ድል ያደረገውን ካሚል ሸምሱን ሳስብ ሀገራችን ሰው እንዳላጣች ማረጋገጫ ይሆነኝና እጽናናለው፡፡

ወዳጄ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ የነጻነት ምልክት ሆነሀልና እንኳን ደስ አለህ! ከምትወዳቸው ቤተሰቦችህ ለመቀላቀል እንኳን አበቃህ፤ ከባለቤትህ ጋር ምን ያህል እንደምትዋደዱ አውቃለው፤ ካምፓስ እያለን ባለቤትህ ውጭ አገር ሆና ስትደውልልህ ‹ተራርቀን እስከመቼ?› ተባብላቹሁ የተላቀሳችሁበትን ጊዜ አስታውሳለው፤ ባለቤትህም እንኳን ከልደታ-ቂሊንጦ-ቃሊቲ ከመመላለስ አረፈች፤ አላህ እንኳን አንድ አደረጋችሁ!!!

በነገራችን ላይ ከሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች መካከል በቀዳማይ ሚኒስትራችን አይተ መለስ ዜናዊ ጥርስ የገባ ሰው ቢኖር ካሚል ሸምሱ ነበር፤ ይህንንም በአፍ ወለምታ የምናገረው ሳይሆን በማስረጃ ነው፤ ካሚል ሸምሱ በተለያየ ጊዜ ለሙስሊሙ ህብረተሰብ መፍትሄ ለማፈላለግ ባደረገው ጥረት በርካታ ስብሰባዎችን መርቷል፤ ታዋቂው ደራሲ አሌክስ አብርሀም ካሚል በሻሸመኔ ከተማ ተገኝቶ ህገ መንግስቱን የተመረኮዘ ማብራሪያ ሲተረጉም የሚያሳይ ምስል በመጽሀፈ ገፁ ለጥፎ ተመልክተናል፡፡

ካሚል ሸምሱ በተደጋጋሚ የሚናገረው አንድ ኃይለ ቃልም ነበር፣ ‹መንግሥት እኛን ወንጀለኛ ብሎ ለማሰር ማስረጃ ሳይሆን መረጃ የለውም› የምትል ነበር፤ የሰዎችን ሀሳብ የራሳቸው እንደሆነ አድርገው ማቅረብ የሚቀናቸው አይተ መለስ ዜናዊ ፓርላማ ላይ እንደ ጎበዝ ተማሪ ከፊት ወንበር ላይ ተሰይመው፤ ‹ኮሚቴዎቹን ለማሰር ማስረጃ መረጃም አለን› ሲሉ ተናገሩ፤ የካሚል ሸምሱ አነጋገር እንቅልፍ ነስቷቸው እንደነበር ራሳቸውን በራሳቸው አጋለጡ፡፡

ጥርስ ውስጥ የገባው ካሚል ሸምሱ ፌዴራል ፓሊስ፣ የደህንነት መስሪያ ቤቱ፣ ኢቲቪ፣ ማእከላዊ፣ ቂሊኒጦና ቃሊቲን የመሳሰሉ የመንግሰት ተቋማት ተባብረው አብጠርጥሮ የሚያውቀውን ሰብአዊ መብት አንድ ሁለት … እያሉ አራቆቱት፡፡ አሸባሪ ነህ ሲሉም ሮቦት ዳኞች ፈረዱበት፤ ከወህኒም ጨመሩት፤ ጊዜ ለኩሉ እንዲል ጠቢቡ ከፍርግርጉ ጀርባ የነበረውን ካሚል ሸምሱ እውነት ነጻ አወጣችው፤ ምናልባትም አንዳንድ የዋሆች ይህንን የህወኃት ድርጊት ‹ምህረት› ብለው ይጠሩት ይሆናል፡፡

አትሳሳቱ ! ኮሚቴዎቻችን የታሰሩት፣ የተሰቃዩትና የተፈረደበቸወ ጥፋተኞች ሆነው እንዳልሆነ ራሱ ወያኔ አሳምሮ ያውቀዋል፤ እነ ካሚል ሸምሱን ነጻ ያወጣቸውም እውነትን ይዘው እስከ መጨረሻው በመጓዛቸው ነው፤ መሀሪ የሚባል የወያኔ አባል ሊኖር ይችላል፤ ወያኔ ግን መሀሪ አይደለም፡፡

(besufekadreje@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule