• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ግንቦት 20 በህግ የታወቀ የህዝብ በዓል ነው?

May 29, 2018 03:44 pm by Editor Leave a Comment

በእኛ ሀገር የሚከበሩ የህዝብ በዓላት በህግ የታወቁ ናቸው። ኢትዮጵያ ውስጥ የሚሠሩ መንግሥትና መንግሥታዊ ያልሆኑ ዓለምአቀፍ ተቋማት እንዲሁም ኢምባሲዎች እና የቆንፅላ ጽ/ቤቶችም የእኛን ሕዝብ በዓላቶች እንዲያከብሯቸው ይጠበቃል። ምክንያቱም በዓላቱን ማክበር ህዝብን ማክበር ከዚያም ሲያልፍ ሀገሪቱ ሉዓላዊ መሆኗን ማረጋገጥ ነውና።

እነዚህ በዓላት የዘመን መለወጫ በዓል (መስከረም 1)፣ የዓደዋ ድል መታሰቢያ ቀን (የካቲት 23)፣ የድል ቀን (ሚያዝያ 27)፣ የዓለም የሠራተኞች ቀን፣ መስቀል (መስከረም 17)፣ ጥምቀት (ጥር 11)፣ የክርስቶስ ልደት(ታህሳስ 29/28) እንዲሁም ቀናቸው በየዓመቱ የሚቀያር ስቅለት፣ ትንሳዔ፣ ፣ኢድ አልአድሃ፣ መውሊድና ኢድ አል ፈጥር ናቸው። በእነዚህ ቀናት እንደሁኔታው የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች፣ የግል ድርጅቶችና የንግድ ሱቆች ለሕዝብ አገልግሎት ዝግ ሲሆኑ ይስተዋላል።

አንድ ሠራተኛ በነዚህ ቀናት ስራ ባይሰራም ቀጣሪው መስሪያ ቤት /ድርጅት/ ሙሉ ደመወዝ እንዲከፍል ህግ ያስገድዳል። ምናልባትም በስራው ባህሪ ምክንያት አንድ ሰው በእነዚህ ቀናት ውስጥ የሚሰራበት ድርጅት የሚያሰራው ከሆነ በልዩ ቀመር ተጨማሪ ክፍያ ቀጣሪ መስሪያ ቤቱ እንዲከፍል የአሰሪ እና ሠራተኛ ህግ ያስገድዳል። የዚህን ዝርዝር አልሄድበትም። የፅሁፍ ዓላማም አይደለም።

ዛሬ (ጽሁፉ ትላንት የወጣ ነበር) ግንቦት 20 ነው። ኢህአዴግ ደርግን ያስወገድኩበት ቀን ነው ይላል። ኢህአዴግ አሁን መንግስት መስርቷል። ዛሬ የህዝብ በዓል ነው በማለት በተለይ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ዝግ ናቸው። አዲስ አበባ ያሉ አንዳንድ ኢምባሲዎች ቀኑን የህዝብ በዓል አድርገው አገልግሎት እንደማይሰጡ ድረገፃቸው ላይ አስቀምጠዋል። ለአብዛኛው ሰራተኛ የእረፍት ቀን ነው።

ግን ለመሆኑ ግንቦት 20 በህግ የታወቀ ከላይ እንደጠቀስኳቸው ዓይነት ደረጃ ያለው የህዝብ በዓል ነው? ለምንስ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች ዛሬ ዝግ ሆኑ? ይህንን ለመመለስ ዋነኛ መሠረታችን በ 1967/75 የሕዝብ በዓላትን እና የእረፍት ቀንን ለመወሰን የወጣው አዋጅ ቁጥር 16/1967 ነው። በዚህ አዋጅ መቼም ደርግ በ1967 ዓ.ም ግንቦት 20፤ 1983 በኢህአዴግ እንደሚወገድ ተንብዮ የህዝብ በዓል ያደርገዋል ተብሎ አይገመትም። (ስለዚህ) አልተካተተምም።

ከ1967 በኋላ የህዝብ በዓላት እና የእረፍት ቀንን በተመለከተ የወጣው ብቸኛ ህግ በ 1988/96 የወጣው አዋጅ ቁጥር 29/1988 ነው። ይህ አዋጅ የበፊቱ ማሻሻያ ነው። ያሻሻለውም አዋጅ 16/1967 አንቀፅ ሶስትን ብቻ ነው። አንቀፅ 3 ደግሞ “የድል ቀን” ስያሜን እና ሚያዝያ 27 መከበር እንዳለበት አድርጎ አሻሽሎታል። ከዚህ ውጭ የማሻሻያ አዋጁ ያለው ነገር የለም። ግንቦት 20ንም እንደ አዲስ በዓል አላካተተም። ታዲያ ግንቦት 20 ከየት መጦ ነው የሕዝብ በዓል የሆነው? ይሄንን አስመልክቶ ከ 1988 በኋላ ህግ ወጥቶ እንደሆን ፈልጌ አላገኘሁም።

በነገራችን ላይ ህግ ስለሌለ ብቻ ሳይሆን እንዲሁ ዝም ብሎ በአመክኖዊ አስተሳሰብ ግንቦት 20 የህዝብ በዓል ሊሆን አይገባውም። ብሄራዊ በዓል እና የድርጅት በዓል መለያየት አለባቸው። ግንቦት 20 የድርጅት በዓል እንጂ ብሔራዊ በዓል አይደለም። ኢህአዴግ እንደ ድርጅት ለራሱ ማክበር ይችላል። መብቱ ነው። የመንግሥት ተቋማትን እና ህዝቡን ግን በህግ ቋንቋ መዝጋት እና ማስገደድ አይችልም።

ነገሩ እንዳለመታደል ሆኖ እኛ ሀገር የፖለቲካ ፓርቲ እና መንግሥት ተቀላቅለዋል። በአሰራር አንድ ናቸው። መከበር አለበት ቢባል እንኳን ኢህአዴግ ህግ ሳይኖር ግንቦት 20 ይከበር ከሚለን ህግ አውጥቶ አክብሩ ቢል ምን ይሳነዋል። ህጉን በፓርላማ ማፀደቅ ይችላል። ሙሉ መቀመጫ እስካለው ድረስ። ያለምንም ህጋዊ መሰረት ይከበር ማለት ግን ህዝብን በትልቁ እንደመናቅ ይቆጠራል። ሰራተኛውም ማረፍ ስለሚፈልግ ቀኑን በስምምነት ዝግ ያደርገዋል። ይሄ ድርጊት በየዓመቱ ተለመደና ግንቦት 20 ብሔራዊ የህዝብ በዓል ሆኖ አረፈው።

ተፈራ ደጉ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Law Tagged With: eprdf, ginbot 20, Left Column, may 28, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule