• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ ፈርስ–ት ባለቤትን ይተዋወቁት!

January 10, 2016 09:27 pm by Editor Leave a Comment

ቤን እባላለሁ። EthiopiaFirst የሚባል ለሕወሓት/ኢሕአዴግ ጭፍን ወገንተኛ ሆኖ የሚሠራ “የሚዲያ” ተቋም አለኝ። EthiopiaFirst የሚለው ያው ደርግ ‘ኢትዮጵያ ትቅደም’ እንዳለው ወይም ናዚዎች ‘ጀርመን ትቅደም’ እንዳሉት ሰው ማባበያ ስያሜ ነው። ኢትዮጵያ ፈርስት እያልኩ የምጠራውን የሚዲያ ተቋምን ተጠቅሜ ኢሕአዴግ የጠላውን ጠልቻለሁ፣ ኢሕአዴግ የወደደውን ወድጃለሁ። ለምሳሌ የዞን፱ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ሲታሰሩ “እሰይ! አገር ሊያተራምሱ ሲሉ ተያዙ” እያልኩ፣ እየማልኩ እና እየተገዘትኩ ፕሮግራም ሠርቼ ተመልካች ለማሳሳት ጥሬ ነበር።

በዜግነቴ ካናዳዊ ነኝ፤ ቢሆንም ግን ለውጭ ዜጎች የማይሰጠው ዕድል የሕወሓት/ኢሕአዴግ ወዳጅ ስለሆንኩ ተሰጥቶኝ አንዳንዴ በየወሩ የሚታተም «ኅብረ–ብዕር» የተባለ መጽሔት ባለቤትና አዘጋጅ ሆኛለሁ። በመጽሔቴ ላይ ‘አብይ ጉዳይ’ የሚባል አምድ አለኝ። አምዱ «…በተመረጠ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ትንታኔ፣ ማብራሪያ የሚሰጥ ከመሆኑም በላይ በጉዳዩ ላይ በቂ ጥናት በማድረግ ወቅታዊ አብይ አጀንዳ ላይ በመመርኮዝ መረጃ የሚቀርብበት ነው»። በዚሁ መሠረት በዚህ ሳምንት (ቅፅ 02፣ ቁጥር 17) ላይ “አዲስ አበባ ስለምን ታወዛግባለች?” የሚል አብይ ጉዳይ ይዤ ወጥቻለሁ። ጽሑፉን ከየት እንዳመጣሁት ታቃላችሁ? እነዛ ‘ኢትዮጵያን ሊያተራምሱ ነበር ያልኳችሁ ጦማሪዎች (በመሀሪ መንግሥታችን ርሕራሄ አሁን ተፈተዋል፣) ከጦማሪዎቹ አንዱ – ዘላለም ክብረት የሚባለው፣ እሱ ጽፎት፣ ከZone9 ጦማር ላይ ሰርቄው ነው። በነገራችን ላይ ግማሹን ነው አሁን ያተምኩት። ግማሹ ደግሞ ለሚቀጥለው እትሜ ገፅ ማሟያ ይሆነኛል ብያለሁ።

በነገራችን ላይ መጽሔቴን ማንም አይገዛልኝም ግን ነፍ የመንግሥትና የግል መሥሪያ ቤቶች ማስታወቂያ ስለሚሰጡኝ ረብጣ እንደጉድ ነው የማፍሰው። የመንጌ ማለትም የመንግሥት ደጋፊ ነኛ! ካላመናችሁ እናንተም ሞክሩት።

ሰሞኑን ደግሞ ፩ኛ – ልክ እንደኔ የሕወሓት ጭፍን ደጋፊ ከሆኑ፣ ፪ኛ – በልባቸው ቢደግፉም/ቢቃወሙም፣ በጋዜጣቸው ገለልተኛ ለመምሰል ከሚሞክሩ፣ እንዲሁም ፫ኛ – ከሕወሓት ጋር የሚያጣላ እውነት ፈፅሞ ከማያቀርቡ ሚዲያ ባለቤቶች ጋር ሆኜ ***የሚዲያ ካውንስል*** በይፋ ላቋቁም ነው። ካውንስሏ ካሁኑ አትራፊ መሆኗ ስለታወቀ ምቀኛ በዝቶባታል። ለወትሮው “እነእከሌ ይታሰሩ” እያልን ስናወራ እና ስንጽፍ ያጨበጭቡልን የነበሩ “ጋዜጠኞች” የካውንስሉ ፕሬዚዳንትነትን ቦታ ሊቀሙኝ እየተስገበገቡ ነው። እኔም በቀላሉ አልፋታቸውም። በሆድ ቀልድ የለማ!

(ምንጭ: BefeQadu Z. Hailu ፌስቡክ ገጽ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule