• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የወገኔ ቅኔ

November 22, 2013 01:48 am by Editor Leave a Comment

እንዲህ እንዲያ ብለው አሙን ፤ ተጠይቀው ሲመልሱ

የወገኖቻችንን ደም ፤ በእብደት ግፍ ያፈሰሱ

የኢትዮጵያ ስደተኞች ፤ ባሕላችንን ተቃረኑ

ንጽሐችንን አረከሱ ፤ ነፍሳችንን አስኮነኑ

መጠጥ በማዘዋወር ፤ በስርቆት ወንጀል በምኑ

አንተ አረመኔ እንስሳ ፤ ምኑን ብየ ላውጣልህ ስም

መጠጥ ምንህ ነውና ፤ ስካርህ የአንተ በሰው ደም

አስገድዳ አልደፈረችህ ፤ ደፈርካት እንጅ በማደም

መድፈርህ ሳያንስ ሳይበቃ ፤ አርደህ በላሃት ርጉም

አንተ ውሉደ አጋንንት ፤ አረመኔ ዘረ ሰዶም ፡፡

    ሌቦች ነበረ ያልካቸው ? እሰይ እንኳንም ሰረቁ

    ፈልገውት እንዳይመስልህ ፤ ምንም ነገር አይደል ድንቁ

    እባክህ ለከት ይኑርህ ፤ በዚህ አይታማም ወገኔ

    ነቢይህ ያውራህ ታሪኩን ፤ ያበሻን ማንነት ብያኔ

    የፍትሕ ደግነት ባለቤት ፤ ሕዝብ እንደሆነ መናኔ

    ነገር ግን እንዲያ ማድረጉ ፤ ሲያደርግ ባላይም በዓይኔ

    የሚነግርህ ስለነበረ ፤ መንገሩ ነበር በቅኔ

    በቋንቋው ጸጋ በዘይቤ ፤ በሰምና ወርቅ ምጣኔ ፡፡

ሐበሻ እንደዚህ ማስኖ ፤ የመከራ ዓይነት ለመጋቱ

ሞት በመንገዱ እየበላው ፤ አሁንም ለስደት መትጋቱ

ውዲቷ ሀገሩን እንደጠላ ፤ እየጣለለት መውጣቱ

ቅድስቲቱን እናት ሀገር ፤ ያረገብንን ያሳር ጓዳ

ለዜጎች ሲዖል ገሃነም ፤ ምቾት የሞላት ለእንግዳ

ሀገር ወገንን አውድሞ ፤ ተግቶ የሚሠራ ለባዳ

ይሄንን ቅጥረኛ መንግሥት ፤ ለጠላት ያደረን ባንዳ

ወልዳቹህ በማሳደግም ፤ ለዚህ ያበቃቹህት ይሁዳ

እናንተው ስለሆናቹህ ፤ የታሪኩ ሀሁ ሠሌዳ

ምሰሶው ወራጅ ማገሩ ፤ መሠረቱና ግድግዳ

ለችግራችን ተጠያቂ ፤ የምስቅልቅሉ ባለዕዳ

እናንተው መሆናቹህን ፤ ሊጠቁምና ሊያስረዳ

ያለንበትን ስንክ አሳር ፤ አውጥቶ ሊያሳይ ከሜዳ

ለማድረግ ነበረ እንጅ ፤ ከቶም አልነበር ሊጎዳ

መናኛ ነገርን ወስዶ ፤ ሊጠቀም ሊሆነው ጋዳ

እናንት በምቾት በቅንጦት ፤ እየኖራቹህ በተድላ

በሠራቹህት ሸር ክፋት ፤ እሱ መዋጡን ባሜኬላ

የስሕተታቹህን ርቀት ፤ የክብደቱንም ልክ ጣራ

ትኩረታቹህን በማግኘት ፤ ሊያሳውቅ እንጅ ያን ዳራ

አነፃፅራቹህ እንድታዩት ፤ በግብረገባዊ ተዋስኦ

በእምነታቹህ ሚዛን ልክ ፤ እንድትለኩት ያለ አድልኦ

ለማድረግ ነበረ እንጅ ፤ ከቶም አይደለም የአመል

የእውነት ምስክር አለን ፤ ከፈላስፋ እስከ አምላክ ቃል ፡፡

    የልቅ ማሰብ ያለባቹህ ፤ ለዚህ ለዚያ ሁሉ ሴራ

    ሀገራችንን ለማፍረስ ፤ ላረጋቹህት ስርሠራ

    ብትከፍሉ የማትጨርሱት ፤ አለባቹህና ብዙ ዕዳ

    ከቶ እንዴት ትሆናላቹህ ፤ አስቡበት አለው ፍዳ

    ይብላኝ ለእናንተ እንጅ ፤ እኔስ አለኝ ሀገር የእርሻ

   ጊዜአዊ ነው የኔ ችግር ፤ ለነገ አለኝ መፈወሻ

   መግቢያ አላጣም እኔ እንዳንተ ፤ አልነቀል መጨረሻ ፡፡

አርቃቹህ ብታስቡ ፤ መኖሪያቹህ ምድረበዳ

እህል ዘርቶ የማያበቅል ፤ የማያቆም አገዳ

አሁን ነገ ላይ ተሟጦ ፤ በሚያልቀው ዘይት ታብዮ

እንዲህ በግፍ ላይ መጫወት ፤ ፍርጃህ ነው የልቅ በል ወዮ

ሐምሳ ዓመታት ለማይቆየው ፤ አቤት ስንቱ ተደረገ

ደጅህ ላይ አለ ጠብቀው ፤ ይነቅልሀል ስደት ነገ

ዘይትህን ሲጨርስ መሬቱ ፤ ሌላ የለው የተነፈገ

ወዴት ይሆን መሰደጃህ ፤ ጎረቤትህ ከመሸገ

ጠላት አርገህ ካቆየኸው ፤ ፊትህን ማየት ካልፈለገ ፡፡

ላለው ሆኖልህ ነገሩ ፤ ዛሬ ላንተ ያደገደገ

ነገ አጠገብህ አይኖርም ፤ በሩን ይዘጋል እያሸገ

ያው በተራህ ትቆጥራለህ ፤ በየዓይነቱ ግፍ ወፍዳ

የዘሩትን ማጨድ አይቀር ፤ አጥቶ መውጫ ቀዳዳ

ወገን ንቃ ይግባህ ሴራው ፤ እኛን ማጥፋት የፈለጉት

እርስ በርስህ እያፋጁ ፤ አስቀምጠው ባንዳ መንግሥት

ሀገርህን ለመውረስ ነው ፤ ሲነጥፍባቸው ሲሳይ ሀብት ፡፡

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

    ብዙ ነው ሴራው ትብትቡ ፤  ምኞታቸውን ለማስመር

    እግዜርን ይዘህ ታገለው ፤ ሳትከፋፈል በብሔር

    ወጥመዱ ይከሽፋል ሴራው ፤ ይወድቁበታል ለአሳር

    የአንተ ቀን ደግሞ ይመጣል ፤ ይኖርህማል አኩሪ ሀገር ፡፡

ኅዳር 2006 ዓ. ም.

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule