• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በውኑ መንፈስ ይታሰራልን?

August 10, 2013 11:47 pm by Editor 2 Comments

እንደ ህወሃት አይነት አምባገነን መንግስታት ከተጠናወታቸው በርካታ ችግሮች መካከል ትግል እና ታጋይን ነጣጥሎ ያለማየት ችግር ሲሆን የትግል መሰረቱ ፍትህ እስከሆነ ድረስ፣የትግል መዳረሻው በተፈጥሮ የተገኘን መብት በችሮታ ካልሰጠናችሁ ከሚሉ አምባገነኖች መዳፍ ፈልቅቆ ለማውጣት እስከሆነ ድረስ በእርግጥም ይህ ትግል ከስጋና ከደም በላይ የተሻገረ በብዙሃን ላይ የሚሰርፅ መንፈስ ነው።ስለሆነም እንደመንፈስ የረቀቀው ትግል በታጋዩ ላይ ገዝፎ ይገለጥ ይሆናል እንጂ ታጋዩ ቢሰዋ አልያም በአምባገነኖች የግዞት እስር ቢወረወር ትግሉ አይታሰርም ደግሞም አይሞትም።

ለምሳሌ ፀረ-አፓርታይድ ትግል ማጠንጠኛው ማህበራዊ፣ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ፍትህን መሻት እንዲሁም የዘረኝነትን ክፉ ቀንበር መሰባበር ነበር።

ነገር ግን በወቅቱ የነበሩ የዘረኛው አፓርታይዳዊ አገዛዝ አመራሮች የትግሉን ረቂቅ ወጣቶችንና አዛውንቶችን ለእስርና ለሞት ከመዳረጋቸው ባሻገር የትግሉን መሪ ኔልሰን ማንዴላን በሮበን ደሴት ላይ ለ27 ዓመታት ሊያስሩ ችለዋል።ይሁን እንጂ የትግሉ መንፈስ ፍትህና ነፃነትን የሚፈልጉትን ሁሉ ኮርኩሮ የመቀስቀስ አቅም ስለነበረው ፀረ-አፓርታይድ ፍልሚያው እንደ ሰደድ እሳት ከያቅጣጫው ይንቀለቀል ነበር።ይልቁንም ታጋዮችን በመስበር ትግሉን እናከስማለን የሚሉትን አምባገነኖች የትግሉ ወላፈን እየበላቸው ዛሬ ከመጥፎ ተሞክሯቸው ጋር ታሪክ ሆነው ቀርተዋል።

በሀገራችን ኢትዮጵያም እየተከሰተ ያለው ሁኔታ ከዚህ ብዙም የሚርቅ አይደለም።ታጋዮችን ላነሳሳቸው የህዝብ ጥያቄ መልስ ከመስጠት ይልቅ በግለሰቦች ላይ የሚደረገው ጥቃት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ ቢመጣም የትግሉ እቶን ይበልጥ ከመንደድ ወደኋላ አላለም።ሠርካለም ፋሲል በግፍ በወህኒ እንድትወልድ መደረጉ እነ ርዕዮት አለሙን ከጋዜጠኝነት አላሸሻቸውም፥ይልቁን ስለእውነት እና ፍትህ በመቆም ለብዙ ወጣቶች አርአያ በመሆን የወያኔን የግፍ ፅዋ በወኔ ተጎነጨችው እንጂ።እስክንድር ነጋን በግፍ በህፃን ልጁ ፊት በካቴና በማሰር ወደ ወህኒ ሲጋዝ፣በውርስ ያገኘውን የእናቱን ቤት መንግስት ሲወርሰው በርግጥም በወያኔ ሹማምንት ስሌት ”እስክንድርን ያየ ይቀጣ” በሚል የህዝብ የነፃነት ጥያቄ በፍርሃት ካባ ተሸፍኖ ይቀራል ከሚል የመነጨ ነበር።

በቀለ ገርባን በማሠር፣ባለቤቱን በግፍ ከሥራ በማፈናቀል የተተኪው ትውልድ አካል የሆኑ ህፃናት ልጆቹን ለችግር  በማጋለጥ የኢትዮጵያን ህዝብ የነፃነት ጥያቄ ማፈን አይቻልም።ይልቁን ዛሬ የትግሉ መንፈስ አድማስን ተሻግሮ የነፃነት ጩኸታችንን በአውሮፓ እና በአሜሪካ መንግስታት ተወካዮች ሳይቀር እየተስተጋባ ይገኛል።በቅርቡ በአውሮፓ ህብረት ፓርላማ  የሰብዓዊ መብት ኮሚቴ አባላት በጀርመናዊቷ ባርባራ ሎክቢለር በመመራት ወደ አዲስ አበባ ያቀና ሲሆን በኢትዮጵያ የሚታየው የሰብዓዊ መብት አያያዝ አሳሳቢ መሆኑን የህሊናና የፖለቲካ እስረኞችን ሁኔታ ለማየት ወደ ቃሊቲ እንዲሄዱ ከተደረገ በኋላ በተለመደው የወያኔ ድራማ ከስፍራው ያለ ውጤት እንዲመለሱ ተደርጓል።

በአንድ ነገር ይበልጥ እርግጠኞች ነን፦እልፎች በወያኔ ግዞት በግፍ ሊጣሉ ይችላሉ፣ አዕላፍት ሊሰው ይችላሉ። ነገር ግን የትግላችን መሠረት የሆነው የነፃነት፣የእኩልነት፣የፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል፣የማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና የፖለቲካዊ ፍትህ ጥያቄያችን ግን ፈፅሞ በግዞት በቃሊቲና መሰል ወኅኒዎች ሊታሠር አይችልም። (ፎቶ: በጸሃፊው የተላከ)

ጸሃፊው በዚህ አድራሻ ይገኛሉ: beyenemesfin77@yahoo.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. አለም says

    August 12, 2013 12:22 am at 12:22 am

    የኢትዮፕያን ሪቪው አታሚ ኤልያስ ክፍሌ እንዴት እዚህ ውስጥ ተገኘ?

    Reply
    • abiti says

      August 12, 2013 11:33 am at 11:33 am

      (ፎቶ: በጸሃፊው የተላከ)

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule